አዲስ ነገር መረጃ
Kanalga Telegram’da o‘tish
#አዲስ_ነገር_መረጃ #መረጃዎች_በትኩሱ ና ሳይዉሉ እንዲሁም ሳያድሩ በቻናሉ በኩል ይደርሳሉ Addis Ababa , Ethiopia Buy Ads : https://telega.io/?r=UbutLo2z #ለአስተያየት እና ለማስታወቂያ ስራዎች 👇👇 @Addisnegermereja_bot
Ko'proq ko'rsatish103 402
Obunachilar
-6824 soatlar
-937 kunlar
+16730 kunlar
Postlar arxiv
የሃይማኖት ነገር ቁሳዊ ሳይሆን መንፈሳዊና በሃይማኖት ሆኖ በመንፈሳዊነት የሚታወቅና የሚታመን ነው።
ሥላሴ፣ ሠለሰ ሶስት አደረገ፤ ካለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን፤ ሥላሴ ማለት ሶስትነት ማለት ነው። ለምሣሌ ሰዎች በጸበል ይድናሉ፡፡ አንዱ ጸበል ሁሉን አይነት በሽታ ይፈውሳል፡፡ በዓለም ሕክምና ግን የአንደኛው መድኃኒት ለአንዱ መርዝ ነው፡፡ መንፈሳዊው ሕክምና ጸበል ግን ጤነኛ ቢጠጣው መጠበቂያ፣ ሕሙም ቢጠጣው ፈውስ ነው፡፡
የሥላሴን አኗኗር በስጋዊ ስሌት የማንመረምረውም መንፈሳዊ በመሆኑ ነው፡፡ የምሥጢረ ሥላሴን ትምህርት ስንማር ከሂሳብ ቀመር ሕግ አስተሳሰብ ነጻ መሆን ያሻል። ምክንያቱም መንፈሳዊዉ ጥበብ ሥጋዊዉን ጥበብ ወይም ፍልስፍና ይመረምረዋል እንጅ መንፈሳዊ ጥበብና ምሥጢር በዓለማዊ ዕውቀትና ምርምር ሊደረስበት አይቻልምና።
በአንድነት በሦስትነት የሚመሰገን፣ ዓለምን ፈጥሮ የሚገዛ አምላክ ቅድስት ሥላሴ፡፡ በዘፍጥረት 18÷1 “እግዚአብሔር በመምሬ ዛፍ ስር ለአብርሐም ተገለጠለት። አብርሐምም ዓይኑን አነሳና ሦስት ሰዎችን አየ” የሚል ቃል አለ፡፡ ይህ ድንቅ ምስጢር እግዚአብሔር በሶስትነቱ በሰዎች አምሳል ለአብርሐም መገለጡን በቁጥር ሶሰት ብሎ ያስረዳል። አንዳንዶች ይህ ሀሳብ ስለሥላሴ አይደለም የሚል ጥያቄ ያነሳሉ፡፡ መጽሐፉ ግን “እግዚአብሔር ከሶስት ሰዎች ጋር ወይም ከሁለት መላእክት ጋር ተገለጠለት” አይልም። ወይም መላእክትም ሆኑ ሰዎች በዚህ ሥም አይጠሩም፤ በኢሳ 42÷8 “እኔ እግዚአብሔር ነኝ፤ ስሜም ይህ ነው! ክብሬን ለሌላ፣ ምስጋናዬንም ለጣዖት አልሰጥም።” ይላልና፡፡ በማያወላዳ ሁኔታ ሦስት ሰዎችን አየ” ብሎ ለይቶ ስለተናገረ እግዚአብሔር ሦስትነት ያለው መሆኑን በግልጽ ያስረዳል።
የቅድስት ሥላሴ ስማቸው ከአካላቸው፣ አካላቸው ከስማቸው ሳይቀድም ከዓለም በፊት የነበረ ስም ነው እንጂ ኋላ የተገኘ አይደለም፡፡ ቅድምናቸው ዘመኑን ቢወስነው እንጂ ዘመኑ ቅድምናቸውን አይወስነውምና፡፡ የእግዚአብሔርን አንድነት በባህርይ፣ በህልውና፣ በፈቃድ፣ በሥልጣን፣ በመፍጠር በመሳሰሉት፡፡ የሰው ነፍስ የቅድስት ሥላሴ ምሳሌ ናት፡፡ ይኸውም አብ በልብ፣ ወልድ በቃል፣ መንፈስ ቅዱስ በእስትፋስ ይመሰላሉ፡፡ በእግዚአብሔርነቱ፤ ልብ፣ ቃል፣ ሕይወት አለ። ነፍስ ሶስት ባህርያት ቢኖሯትም አንድ እንደምትባል እግዚአብሔርም ሶስት ስም፤ ሶስት ግብር፤ ሶስት አካል፤ ቢኖረውም አንድ አምላክ እንጅ ሶስት አማልክት አይባልም፡፡ ሥላሴ የሚለው ስም የአንድነትና የሶስትነት ስም ነው፡፡ በስም፣ በግብርና በአካል ሶስት እንላለን፡፡
በመዝሙር 138÷7 እንደተጻፈው በሁሉ የመላ ነውና፡፡ “ከመንፈስህ ወዴት እሔዳለሁ፤ ከፊትህስ ወዴት እሸሻለሁ ወደ ሰማይ ብወጣ አንተ በዚያ አለህ፤ ወደ ውቅያኖስም ጥልቅ ብወርድም በዚያ ትገኛለህ፤ እንደ ንስር የንጋትን ክንፍ ብወስድ ከአጽናፍ አጽናፍ ብበርም እጅህ በዚያ ትመራኛለች ቀኝህም ትይዘኛለች” ይላል፡፡ ለአብ፣ ለወልድ፣ ለመንፈሰ ቅዱስ ለየራሳቸው ፍፁም ገጽ፣ ፍፁም መልክ፣ ፍፁም አካል፣ አላቸው። አካል በአጠቃላይ ሙሉው የሰውነታችን ክፍል ነው። የፍጡራን አካል የሚታይ፣ የሚዳሰስ፣ የሚመጠን፤ የሚወሰን፣ ሲሆን የሥላሴ አካል ግን፤ የማይታይ ፣ በእጅ የማይዳሰስ፣ በቦታ የማይወሰን፣ በሁሉም ምሉዕ ነው። የቅድስት ሥላሴ ምሕረትና ቸርነት አይለየን፡፡
ገዳማውያኑ ይህን ምሕረትና ቸርነት ተስፋ አድርገው ይተጋሉና ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
❤ 42🙏 5🤪 4
የሱዳን ቀውስ፡ በወርቅ እያበራ፣ በረሃብ እያለቀሰ
ሱዳን በዘር ማጽዳት፣ አስገድዶ መድፈር፣ 4.3 ሚሊዮን የሚሆኑ የተፈናቀሉ ሰዎች እና በከባድ የምግብ ቀውስ የተመታች የአፍሪካ ሀገር ነች።
በሱዳን ባለው የዘለቀው የእርስ በእርስ ጦርነት ምክንያት ቢያንስ 150,000 ሰዎች ተገድለዋል። በዚህ ሁኔታ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሱዳንን በዓለም ላይ እጅግ የከፋ ሰብአዊ ቀውስ ያለባት ሀገር አድርጎ አውጇል።
በዚህች ሀገር ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ ማዕድናት ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩ ቶን ወርቅ አለ።
በተጨማሪም፣ በነዳጅ በበለፀገችው ሱዳን ውስጥ በእነዚህ በጥቁር ገበያ በተሸጡት ሀብቶች የተገኘው ገንዘብ በርስ በእርስ ጦርነቱ ውስጥ ሚና እየተጫወተ ነው። ወርቁ ቢኖርም በአስተዳደር መጓደል እና በስልጣን ሽኩቻ ምክንያት በሀገሪቱ ውስጥ ቢያንስ 2.5 ሚሊዮን ሰዎች በረሃብ እየተሰቃዩ ነው።
የሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት ታሪክ
ሱዳንከፈረንጆቹ እስከ 1956 ድረስ በእንግሊዝ እና በግብፅ ትተዳደር ነበር። በግብፅ እርዳታ ሀገሪቱ ጥር 1956 ነፃነቷን አገኘች። ከዚያ በኋላ በደቡብ ሱዳን እና በአሁንዋ ሱዳን መካከል የዘር እና የሃይማኖት ግጭት የነበረ ሲሆን ረጅም ግጭት ተፈጠረ። በ1983 ፕሬዝዳንት ጃዓፋር ኑማን የእስልምናን ሸሪዓ ህግ ሲያስተዋውቁ ከደቡብ ሱዳን ጋር ከባድ የእርስ በእርስ ጦርነት ተጀመረ።
በዚህ ሁኔታ የሱዳን ወታደራዊ እና እስላማዊ የፖለቲካ መሪዎች ያቀዱት መፈንቅለ መንግስት ተካሄደ። ኦማር አልበሽር ሰኔ 1989 በመፈንቅለ መንግስቱ ሱዳን ውስጥ ስልጣን ያዙ። በወቅቱ አልበሽር በሱዳን ጦር ሰራዊት ደህንነት ውስጥ ከፍተኛ ደረጃ ያለው መኮንን ነበሩ። መፈንቅለ መንግስቱን የመሩት እሳቸው ነበሩ።
ነገር ግን በ2019 አልበሽር አሰቃቂ እጣ ፈንታ ውጤቶችን መቀበል ነበረባቸው። በ2019 በሱዳን በእርሳቸው ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ ተነሳ። በዚህም ምክንያት ጦር ሠራዊቱ በሌላ መፈንቅለ መንግስት ፕሬዝዳንቱን ገለበጠ። ሆኖም፣ ተራው ሕዝብ ዲሞክራሲ እንሰፍን በመጠየቅ ተቃውሞውን ቀጠለ። በተቃውሞው ጫና የሠራዊቱና የሲቪል አስተዳደሩ በጋራ ተነሳሽነት መንግሥት የተቋቋመ ቢሆንም፣ ያ መንግሥትም በጥቅምት 2021 በሌላ መፈንቅለ መንግስት ተወገደ።
ከመፈንቅለ መንግስቱ ጀርባ የነበሩት ሁለቱ ዋና ዋና ሰዎች ጄኔራል አብደል ፋታህ አል-ቡርሃን እና ጄኔራል መሐመድ ሃምዳን ዳጋሎ ናቸው። ጄኔራል አል-ቡርሃን የሱዳን የታጠቁ ኃይሎች (ሠራዊቱ) መሪ እና የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ናቸው። ሃምዳን ዳጋሎ የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች (RSF) አዛዥ ናቸው። በአለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች መሠረት፣ ይህ መጥፎ ስም ያተረፈው ከፊል ወታደራዊ ኃይል (RSF) በሱዳን ውስጥ የተለያዩ ሰብአዊ ወንጀሎችን እየፈፀመ ነው። የቡርሃን እና የዳጋሎ ኃይሎች ለሱዳን ቀውስ ተጠያቂ ናቸው።
የጦርነቱ ዋና አቅርቦቶች ወርቅ እና ነዳጅ ናቸው
በሱዳን ውስጥ በተገኙ የተለያዩ ማዕድናት ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩ ቶን ወርቅ ተከማችቷል ተብሎ ይነገራል። በተጨማሪም፣ ተጨማሪ ማዕድናት ሳይገኙ አሉ ። በሱዳን ውስጥ ትልቁ የወርቅ ማዕድን ቦታ ጀበል አመር ነው። ማዕድኑ በቀጥታ በRSF ቁጥጥር ስር ነው። ከዳጋሎ ቤተሰብ ጋር የተቆራኘው አል-ጁናይድ ኩባንያ ማዕድኑን ሲያስተዳድር ቆይቷል። በተጨማሪም በዳርፉር እና በደቡብ ኮርዶፋን ክልሎች ውስጥ የሚገኙት አብዛኛዎቹ የወርቅ ማዕድናት በአሁኑ ጊዜ በRSF ቁጥጥር ስር ናቸው።
በ2024 RSF ከእነዚህ ማዕድናት ቢያንስ 10 ቶን ወርቅ አውጥቷል፣ የገበያ ዋጋውም 860 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ነው። ሁለቱ ትልልቅ ገዢዎች የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች እና ግብፅ ናቸው። ከዚህ ወርቅ ውስጥ 80 በመቶው በህገ-ወጥ መንገድ ይዘዋወራል። ለህገ-ወጥ ዝውውር በጣም የታወቀው መንገድ ከዳርፉር ድንበር ክልል ወደ ግብፅ በኢትዮጵያ በኩል ነው።
ሌላው ከዳርፉር ድንበር ክልል ወደ ሊቢያ ከዚያም ወደ ኤሚሬትስ ነው። በተጨማሪም RSF በታኅሣሥ መጀመሪያ የሱዳንን ትልቁ የነዳጅ መስክ የሆነውን ሄግሊግን ተቆጣጥሯል። ዜጎችን ለመግደል እየዋለ ያለው መሳሪያ በወርቅና በነዳጅ ገንዘብ እየተገዛ ነው።
አስከፊ ሰብአዊ ቀውስ እና የዋጋ ግሽበት
ግጭቱ በመላው ሱዳን ከ150,000 በላይ ሰዎችን ገድሏል። ረሃብ በሀገሪቱ ተስፋፍቷል። ወደ 12 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ቤታቸውን ለቀው ለመሰደድ ተገደዋል። በመቶዎች የሚቆጠሩ ሴቶችም ተደፍረዋል።
ዓለም አቀፉ የስደት ድርጅት (IOM) እንደገለጸው በሱዳን ውስጥ 30 ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች በአሁኑ ጊዜ ሰብአዊ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል። ከእነዚህ ውስጥ 9.6 ሚሊዮን የሚሆኑት በውስጥ ተፈናቃዮች ሲሆኑ፣ 4.3 ሚሊዮን የሚሆኑት ደግሞ ወደ ጎረቤት አገሮች ተሰደዋል።
በተጨማሪም ከ700,000 በላይ ሕጻናት በከፍተኛ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት እየተሰቃዩ ሲሆን ከ2.4 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ደግሞ የረሃብ አደጋ ተጋርጦባቸዋል።
ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ የሱዳን ፓውንድ ያለማቋረጥ ዋጋው እየቀነሰ ነው። በ2025 በሀገሪቱ የዋጋ ግሽበት 113 በመቶ ደርሷል።
የዩኒሴፍ ባለስልጣን ቴድ ቻይባን እንደተናገሩት በችግሩ በከፋ ሁኔታ የተጎዱት ህጻናት ናቸው። ወደ 1.4 ሚሊዮን የሚጠጉ ህጻናት በረሃብ ስጋት ውስጥ ሲሆኑ፣ 14 ሚሊዮን የሚሆኑት ደግሞ ከትምህርት ገበታ ውጪ ናቸው፣ ይህም በሱዳን ውስጥ ካሉት ህጻናት አራት አምስተኛው ነው። በሰሜን ዳርፉር ብቻ በዚህ ዓመት 150,000 ሕጻናት በከፍተኛ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት እየተሰቃዩ ነው።
ምንጭ፡ ሚድል ኢስት ሞኒተር/ቢቢሲ/አልጀዚራ
@Addis_News
@Addis_News
❤ 23😢 12
Photo unavailableShow in Telegram
ከ5 ሺህ በላይ የኢትዮጵያ ዜጎች በአዲሱ የአሜሪካ ውሳኔ ተጠቂ ይሆናሉ ተባለ
አሜሪካ ከሰሞኑ ለኢትዮጵያውያን ዜጎች ትሰጥ የነበረውን ጊዜያዊ የህግ ከለላ ማቋረጧን ተከትሎ 5ሺ ኢትዮጵያውያን የውሳኔው ተጠቂ እንደሚሆኑ ታውቋል፡፡
ቀደም ሲል 5001 ኢትዮጵያውያን በቀድሞው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ዘመን የህግ ከለላ ተሰጥቷቸው እንደነበርና 263 የሚሆኑ ተጨማሪ ዜጎች አመልክተው በመጠባበቅ ላይ እንደነበሩ ተገልጿል፡፡
አሜሪካ በፈረንጆቹ ታህሳስ 12ቀን 2022 በኢትዮጵያ የነበረውን ግጭት ተከትሎ ለኢትዮጵያ ዜጎች ጊዜያዊ የህግ ከለላ መስጠት መጀመሯ የሚታወስ ሲሆን በሚያዚያ 2024 ዳግም ተራዝሞ እንደነበር ይታወቃል፡፡
ይሁን እንጂ ስደተኛ ጠል ነው የሚባለው የትራምፕ አስተዳደር ከሰሞኑ ይፋ ባደረገው ውሳኔው ለእነዚህ ኢትዮጵያውያን የተሰጠውን ከለላ አንስቷል፡፡
@seledadotio
@seledadotio
Photo unavailableShow in Telegram
ሕፃናት በ12 ዓመታቸው የሞባይል ስልክ እንዲጠቀሙ መፍቀድ የሚያስከትለውን ጉዳት ያውቃሉ❓
ሕፃናት በ12 ዓመታቸው የሞባይል ስልክ (ስማርት ስልክ) እንዲይዙ እና እንዲጠቀሙ መፍቀድ ልጆቹን ለድባቴ እንዲዳረጉ፣ ከመጠን በላይ ለሆነ ውፍረት ታጋላጭ እንዲሆኑ እና ለእንቅልፍ እጦት እንደሚዳርጋቸው አንድ ጥናት አመልክቷል።
አዳጊዎች በረጅም ጊዜ ሂደት የአዕምሮ ዕድገት እና ጤና በተመለከተ ከ2018 እስከ 2020 ባለው ጊዜ ከ10 ሺህ ሰዎች መረጃ በመሰብሰብ ነበር ጥናቱ በአሜሪካ ብሔራዊ የጤና እንስቲቲዩት ድጋፍ የተከናወነው።
በካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ የፊላደልፊያ የሕፃናት ሆስፒታል እና የኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲዎች በጋራ በመሆን ነበር ሕፃናት የሞባይል ቴክኖሎጂ እንዲጠቀሙ መፈቀድ የሚያስከትልው ጉዳት ምንድነው የሚለውን ጉዳይ ለመለየት እና የመፍትሔዎችን ለመጠቆም ጥናቱን ሲያከናውኑ የቆዩት።
ዩኒቨርሲቲዎቹ ዕድሜያቸው 12 ዓመት የሆኑ ሕፃናት ዘመናዊ ስልክ እንዲጠቀሙ መፍቀድ ከአእምሮ በሽታ እና ከመጠን በላይ ውፍረት ቀጥተኛ ግንኙነት እንዳለው በዚሁ በሠሩት ጥናት ማረጋገጥ ችለዋል።
❤ 23
Photo unavailableShow in Telegram
.
በሌሎች ሰወች ፖስት የተደረጉ ያገለገሉ እቃዎችን ፎቶ ፣ አድራሻ ፣ ዋጋ እና የእቃውን ባለቤት ስልክ ቁጥር በ ET Creatives በቀላሉ ያገኛሉ
✅ JOIN 👉 https://t.me/ET_Creatives_Family
ET Creatives
🔥 1
" ከዛሬ ጀምሮ ትምህርት ቤቶች ላልተወሰነ ጊዜ ይዘጋሉ፤ ትራንስፖርትን ጨምሮ ለበሽታዉ አስጊ የሆኑ እንቅስቃሴዎች ላይ ገደብ ጥለናል" - የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር
በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ በማርበርግ ቫይረስ ስጋት ምክንያት ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ ሕዝብ የሚሰበሰብባቸዉ የትራንስፖርት እና የመዝናኛ ቦታዎች ላይ ዕገዳ መጣሉን የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ኡመር ኖኩዌ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በአከባቢው አንድ ሰዉ በቫይረሱ ምክንያት ሕይወቱ ማለፉን ተከትሎ ዉሳኔው መተላለፉን የገለፁት ምክትል አስተዳዳሪዉ በወረዳው ዋና አስተዳዳሪ የሚመራ ግብረሃይል ተወያይቶ ዉሳኔ ማስተላለፉን ገልፀዋል።
በዚህም መሠረት በወረዳዉ የሚከተሉት ጉዳዮች ላይ ዕገዳና ክልከላ መጣሉን አቶ ኡመር ገልፀዋል።
በዚህም መሰረት ፦
➡️ ትምህርት ቤቶች ላልተወሰነ ጊዜ ዝግ ሆነው ይቆያሉ፤
➡️ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት እንዳይሰጡና የሁለት እግር ሞተር ሳይክሎችም ከአሽከርካሪው ውጪ ሁለተኛ ሰው ላልተወሰነ ጊዜ መጫን አይችሉም፤
➡️ ሰርግ፣ ምረቃ፣ ድግስና በሀዘንም ህዝብ ሊያሰባስቡ የሚችሉ ሁኔታዎችም ላልተወሰነ ጊዜ እንዲቆሙና ቀብር በጤና ባለሙያዎች ስምሪት ብቻ እንዲከናወን፤
➡️ ዲ ኤስ ቲቭ (Dstv) ጨምሮ ፑል ቤቶች፤ ቤቲንግ ቤቶች እንዲሁም የምሽት ዳንስ ቤቶች፣ ጫት ቤቶች ላልተወሰነ ጊዜ ተዘግተው እንዲቆዩ፤
➡️ ሰዎች በቡድንና በብዛት የሚሳተፉባቸዉ ማንኛውም አይነት ስፖርታዊ ውድድሮች በወረዳዉ እንዳይካሄዱ ዉሳኔ መተላለፉን አብራርተዋል።
Via : tikvah
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤ 24😢 2👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
ዜና፡ ቲክቶከሩ አዶናይ ከፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር መፈታቱ ተሰማ!
ለአዶናይ አድናቂዎች መልካም ዜና
አዲስ አበባ – በማኅበራዊ ሚዲያ በስፋት የሚታወቀው ቲክቶከር አዶናይ በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ ከቆየ በኋላ አሁን ከእስር መፈታቱን የቅርብ ምንጮች አመለከቱ።
መረጃው ይፋ የተደረገው በአዶናይ የቅርብ ሰው አማካኝነት ሲሆን፣ ድምፃዊ መርከብ ቦኒቷ ፋስት መረጃ ጉዳዩን አረጋግጠዋል ተብሏል።
ይህ ዜና ለቲክቶከሩ አድናቂዎች እና የማኅበራዊ ሚዲያ ተከታታዮች ደስታን የፈጠረ ትልቅ ዜና ሆኗል::
@seledadotio
@seledadotio
❤ 107🤪 11👏 5🥱 5🔥 1💔 1
ባርሴሎናን ለመግዛት 10 ቢሊዮን ዩሮ ያዘጋጁት የሳዑዲው ልዑል
የሳዑዲው ልዑል መሀመድ ቢን ሰልማን ከአውሮፓ ታላላቅ ቡድኖች አንዱ የሆነውን ባርሴሎናን ለመግዛት 10 ቢሊዮን ዩሮ እንዳዘጋጁ ተነግሯል።
በእንግሊዝ ኒውካስል ዩናይትድን የሚያስተዳድረው የሳዑዲ ኢንቨስትመንት ግሩፕ አሁን ደግሞ ከፕላኔታችን ሀያል ቡድኖች አንዱ የሆነውን ባርሴሎናን ለመግዛት ፍላጎት ማሳየቱ ተዘግቧል፡፡
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በገጠመው የገንዘብ ቀውስ ከተቀናቃኞቹ ሪያል ማድሪድ፣ ፒኤስጂ እና ማንችስተር ሲቲ መፎካከር ያልቻለው የካታላኑ ክለብ በመካከለኛው ምስራቅ ባለሀብቶች እይታ ውስጥ ገብቷል፡፡አሁን ላይ ለተጫዋቾች ዝውውር ያልከፈለው በቢሊየን የሚቆጠር ፓውንድ እዳ ያላበት ክለቡ በልዑሉ እጅ ከገባ የአለማችን ውዱ ክለብ ይሆናል፡፡
ክለቡ የቱንም ያክል የገንዘብ ቀውስ ቢገጥመው ከእግር ኳስ ባለፈ የካታሎንያ የነጻነት ምልክት ሆኖ የተሰራ መሆኑ ምን አልባትም መሀመድ ቢን ሰልማን ባርሴሎናን የመግዛት ፍላጎታቸው ችግር ሊገጥመው ይችላል ተብሏል፡፡
ክለቡ ለውጭ ባለሀብቶች ይሸጣል ወይስ ባርሴሎናን ከገባበት የገንዘብ እዳ ለማላቀቅ የስራ ሃላፊዎቹ ሌላ አማራጭ ይጠቀማሉ የሚለው በቀሪ ቀናቶች መልስ የሚያገኝ ይሆናል፡፡
የመካከለኛው ምስራቅ ባለሀብቶች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአለም የእግር ኳስ ውስጥ በጥልቀት በመሳተፍ ላይ የሚገኙ ሲሆን በተለይ እንደ ክሪስቲያኖ ሮናልዶ አይነት ስም ያላቸው ተጫዋቾች ወደ ሳዑዲ ፕሮ ሊግ ማምራታቸው ሳዑዲ ለእግር ኳስ የሰጠችውን ትኩት በሚገባ የሚያሳይ ነው፡፡
@Addis_News
@Addis_News
❤ 19👍 5🤪 5🤣 3
Photo unavailableShow in Telegram
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በየሁለት ሳምንቱ ለማካሄድ ባስቀመጠው ዕቅድ መሠረት 12ኛውን ዙር የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ነገ ማክሰኞ ታህሳስ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. እንደሚያካሂድ አስታውቋል።
ባንኩ በዚህ ዙር ለጨረታ ያቀረበው አጠቃላይ የገንዘብ መጠን 50 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ሲሆን፤ ይህም በ11ኛው ዙር ከቀረበው መጠን ጋር ተመሳሳይ ነው።
በቅርቡ ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም. በተካሄደው 11ኛዉ ዙር የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ላይ፣ የኢትዮጵያ ብር በዶላር ላይ በሁለት ወራት ውስጥ ከ11 በመቶ በላይ ተዳክሞ፣ የምንዛሪ ተመኑ 1መቶ54 ብር መድረሱን ካፒታል ጋዜጣ መዘገቡ ይታወሳል።
@seledadotio
@seledadotio
❤ 11😢 3🤪 3
Photo unavailableShow in Telegram
ዜጎቻችሁን ተቀበሉኝ - ምያንማር
የምያንማር መንግስት ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ ሃገራት ዜጎቻቸውን እንዲቀበሉት ጥያቄ አቅርቧል።
ምያንማርን እያስተዳደረ የሚገኘው ወታደራዊ መንግስት በማጭበርበሪያ ካምፖች የያዛቸውን የውጪ ሃገራት ዜጎች ሃገራቱ እንዲቀበሉት ጠይቋል።
በቅርቡ በታይላንድ ድንበር አካባቢ በተደረጉ ዘመቻዎች በርከት ያሉ የውጪ ሃገራት ዜጎች መያዛቸው ሲታወስ እነዚህን የያዛቸውን ለመቆጣጠርና ለማስተዳደር ስለተቸገረ የዜጎቹ ሃገራት በተቻለ ፍጥነት ቶሎ እንዲቀበሉ ምያንማር ጠይቃለች።
ምያንማር ዘመቻው ባለፈው ጥር ከተጀመረ ወዲህ ከ47 ሃገራት የተውጣጡ 13,272 የውጪ ሃገራት ዜጎችን መያዟን ስትገልፅ አብዛኞቹ ወደ ሃገራቸው ተመልሰው አሁንም 1655 ያህሉ እዛው እንደሆኑ ገልፃለች።
ከቀሩት መካከል ከ500 የሚበልጡት የቻይና ዜጎች ሲሆኑ ከ100- 300 የሚደርሱ #የኢትዮጵያ ዜጎች እንደዚሁም የቬትናም፣ የኬንያ፣ የኢንዶኔዥያ እና የህንድ ዜጎችም እንዳሉ ምያንማር አስታውቃለች።
ምያንማር አብዛኞቹ ወደ ሃገራቸው ያልተላኩ የአፍሪካ ሃገራት ዜጎች ሃገራቸው በታይላንድም ይሁን በምያንማር ኤምባሲ ስለሌላቸው ነው ብላለች።
ምያንማር በአመት 40 ቢሊየን ዶላር ለወንጀለኛ ቡድኖች የሚያስገኙ የማጭበርበሪያ ካምፖች መፍለቂያ ስትሆን ኢትዮጵያን ጨምሮ የበርካታ ሃገር ዜጎች ተታለው በካምፖቹ በግዳጅ እንዲሰሩ ይደረጋሉ።
@Addisinsider_ETH
@Addisinsider_ETH
❤ 22👍 6
አሸዋ ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ከባድ የጭነት ተሽከርካሪ ባደረሰዉ አደጋ የአንድ ቤተሠብ አባላት የሆኑ አራት ሕፃናት እና የአሽከርካሪው ህይወት አለፈ
የባሌ ዞን ዲንሾ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት የትራፊክ ደህንነት እና ቁጥጥር አስተባባሪ ምክትል ኢንስፔክተር ያሬድ ታደሰ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ታህሳስ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ አስራ አንድ ሰዓት ከአርባ ላይ አሸዋ የጫነ ከባድ ተሽከርካሪ ባደረሰው አደጋ የአንድ ቤተሠብ አባላት አራት ሕፃናት እና አሽከርካሪው ሕይወታቸው ማለፉን ገለፁ።
የሰሌዳ ቁጥር ኮድ3 52420 ኢቲ የሆነ ዩዲ የጭነት ከባድ ተሽከርካሪ ከአሳሳ ከተማ አሸዋ ጭኖ ወደ ባሌ ዲንሾ ወረዳ ሀዋ ቀበሌ በተባለ ስፍራ መንገዱን ስቶ የሰው ግቢ ውስጥ በመግባት ሶስት ወንድ እና አንድ ሴት ልጅን ጨምሮ በአጠቃላይ አራት የአንድ ቤተሰብ ላይ ባደረሰው አደጋ አሽከርካሪውን ጨምሮ የአምስት ሠው ህይወት ማለፉን ገልፀዋል።dagu
@seledadotio
@seledadotio
😢 45❤ 18💔 4
Photo unavailableShow in Telegram
🚨ውፍረት መጨመር ይፈልጋሉ❓❓
+251964593642
✔ ከአንድ ወር እስከ 45 ቀን ዉስጥ
ክብደት መጨመር የሚረዳ
✔ የምግብ ፍላጎት መጨመር የሚያስችል
✔ የቆዳን ጥራት እና ልስላሴ ለመጨመር
የሚረዳ
✔ ምንም አይነት የጎንዮሽ ጉዳት የሌለዉ ፤
ለቀጭን ሰዎች የሚመከር
✔ ለሴቶችም የተስተካከለ አቋም
እንዲጎናፀፉ የሚያግዝ
✔ ለወንዶችም ለሴቶችም የሚሆን አለን ፤
🚴♂ያሉበት እናደርሳለን
------------------------------------
ለበለጠ መረጃ ☎️ +251964593642
+251906495051
+251907495051
Telegram: 📥 t.me/AM_CS
t.me/AM_CS1
t.me/AM_CS2
------------------------------------
❤ 7👍 2
በፍቅርም ሆነ በትዳር ግንኙነት ውስጥ ስምምነት እንዲሰፍን የሚጠቅመው የ5 ለ1 ቀመር
ባልና ሚስቶችን ደስተኛ የሚያደርጋቸው ምንድን ነው?
መልሱ በቀላል ቀመር ውስጥ ይገኛል፦ ለእያንዳንዱ አሉታዊ መስተጋብር፣ ቢያንስ አምስት አዎንታዊ መስተጋብሮች ሊኖሩ ይገባል። ትናንሽ ምልክቶችና ዐውቆ በሚወሰዱ ውሳኔዎች ግንኙነታችሁን እንዴት ማጠናከር እና የበለጠ መቀራረብ መፍጠር እንደምትችሉ ይወቁ!
በስነ-ልቦና ባለሙያው ጆን ኤም. ጎትማን አገላለጽ፣ ለረጅም ጊዜ የሚዘልቁ እና ደስተኛ የሆኑ ግንኙነቶች በቀላል ሕግ ላይ የተመሰረቱ ናቸው፦ ለእያንዳንዱ አሉታዊ መስተጋብር፣ ቢያንስ አምስት አዎንታዊ መስተጋብሮች መከተል አለባቸው። እኚህ የሥነ ልቦና ባለሙያ ከሮበርት ደብሊው. ሌቨንሰን ጋር በ 1970 ዎቹ ያገኙት ይህ ግንዛቤ፣ ስለ ግንኙነቶች ያለውን ግንዛቤ በመሠረቱ ለውጦታል።
ሁለቱ ተመራማሪዎች ጥንዶች ግጭቶችን የሚፈቱበትን መንገድ በመመልከት ብቻ ጥንዶቹ አብረው ይቆያሉ ወይስ ይለያያሉ የሚለውን ከ 90 በመቶ በላይ ትክክለኛነት መተንበይ ችለዋል።
የ 5:1 ሕግ ለእርስዎ ምን ማለት ነው?
የጸኑ ግንኙነቶች እንኳን የአሉታዊ ጊዜያት ድርሻ አላቸው። ይሁን እንጂ፣ ቁልፉ ያለው በሚሰጡት ምላሽ ላይ ነው። ጎትማን እንደ ቁጣ ያሉ አሉታዊ ስሜቶች የሚጎዱት በትችት፣ በንቀት ወይም በጥላቻ ሲታጀቡ ብቻ እንደሆነ አጽንኦት ሰጥተው ይናገራሉ።
በሌላ በኩል፣ አዎንታዊ ምልክቶች እና መስተጋብሮች ውጥረትን ለመቀነስ፣ ርኅራኄን ለማሳየት እና የአድናቆት መንፈስ ለመፍጠር ይረዳሉ።
በተለይም በቅርቡ ብዙ ትችት ወይም ጥቃቅን ኃጢአት መፈለግ ከነበረ፣ ከሚከተሉት ነጥቦች ውስጥ በተቻለ መጠን ብዙዎቹን በዕለት ተዕለት ግንኙነታችሁ ውስጥ ለማካተት ሞክሩ።
በግንኙነታችሁ ውስጥ ለበለጠ አዎንታዊነት የሚረዱ ስምንት ምክሮች
1. ቀልድ ይጠቀሙ
ሳቅና ጨዋታ ውጥረትን ለመቀነስ ከትዳር ጓደኛችሁ ጋር ያለውን ትስስር ለማጠናከር ይረዳል።
2. ፍላጎት ያሳዩ
የትዳር ጓደኛችሁን በጥሞና አዳምጡ። በተለይም አስቸጋሪ በሆኑ ጊዜያት ውስጥ ስሜቷን/ ስሜቱን በተመለከተ እውነተኛ ፍላጎት አሳዩ።
3.በየቀኑ ቢያንስ ትንሽ ፈገግታ አይለዮት
በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ ያሉ ትናንሽ ምልክቶች
እንደ አፍቃሪ እይታ፣ ምስጋና ወይም ትንሽ አስገራሚ ነገር ያሉ ትናንሽ ምልክቶች ትልቅ ተጽእኖ አላቸው እንዲሁም ግንኙነታችሁን በረጅም ጊዜ ያጠናክራሉ።
4. ይቅርታ ይጠይቁ ።ሩኅሩኅ ይሁኑ
እውነተኛ ይቅርታ እና ርኅራኄ የትዳር ጓደኛችሁን ስሜት በቁም ነገር እንደምትመለከቱ እና እንደምታደንቁ ያሳያሉ።
5. የጋራ የሆኑትን ነገሮች አጽንኦት ይስጡ
በውይይቶች ላይ፣ በምትስማሙባቸው ነጥቦች ላይ አተኩሩ። ይህ ችግሮችን በቀላሉ ለመፍታት የሚያስችል መሠረት ይፈጥራል።
6. ሌሎች አመለካከቶችን ይቀበሉ
ሁልጊዜ ከእርሷ ጋር ባትስማሙም እንኳ፣ የትዳር ጓደኛችሁን አመለካከት ማክበርና መቀበል አስፈላጊ ነው።
7. ዐውቆ ማድነቅ
ትችትን ለማመጣጠን እና ግንኙነቱን ለማጠናከር በትዳር ጓደኛችሁ ጥንካሬዎችና አዎንታዊ ባህሪያት ላይ ትኩረት ያድርጉ።
8. ፍቅርን ይግለጹ
እንደ ማቀፍ፣ ለስለስ ያለ ፈገግታ ወይም የሚያጽናና ቃል የመሳሰሉ የመቀራረብ ምልክቶች ውጥረትን ሊቀንሱና በእናንተ መካከል ያለውን ትስስር ሊያጠናክሩ ይችላሉ።
✨ ምስጋናዎች፦ ለትልቅ ስምምነት ቁልፍ ናቸው
ምስጋና እና እውቅና ለተሟላ ግንኙነት አስፈላጊ ናቸው። በግለሰቦች መካከል ባሉ ግንኙነቶች ላይ ባለሙያ የሆኑት አርተር ሲ. ብሩክስ ሰዎች በአዎንታዊ አስተያየት አማካኝነት እንደሚያድጉና ዋጋ እንዳላቸው እንደሚሰማቸው አጽንኦት ሰጥተው ይናገራሉ። ስለዚህ፣ የትዳር ጓደኛችሁን አድናቆት በመደበኛነት በማሳየት፣ በፍቅር የተሞላ እና ደጋፊ መንፈስ ትፈጥራላችሁ።
🔑 ማጠቃለያ፦ ለረጅም ጊዜ የሚቆይ ደስታ ቁልፍ
የ 5:1 ሕግ የሚያሳየው ደስተኛ አጋርነት የአጋጣሚ ጉዳይ እንዳልሆነ ነው። እሱ የሚመጣው ከዐውቆ ከሚወሰዱ ውሳኔዎችና የጋራ አድናቆት ነው። በአዎንታዊ መስተጋብሮች ላይ በማተኮር፣ በፍቅር የተሞላና የተሟላ ግንኙነት ለማድረግ መሠረት ትጥላላችሁ።
@Addis_News
@Addis_News
❤ 26👍 4
Photo unavailableShow in Telegram
እንግሊዝኛ ቋንቋን ቤትዎ ቁጭ ብለው ይማሩ
Mark Language Academy
የእንግሊዝኛ ቋንቋ የመናገር ክህሎትዎን ወይም ችሎታዎን የትም ሳይሄዱ ቤትዎ ቁጭ ብለው Face to Face በ Zoom, በቴሌግራም Video Call ወይም Google meet ላይ መማር ይችላሉ
እንዲሁም አስገራሚ ለውጥ ያመጣሉ
✅ Speaking ( ንግግር)
✅ Listening ( ማዳመጥ)
✅ Grammar ( ሰዋሰው )
✅ How to read and Write ( መፃፍ ና ማንበብ )
ሁሉንም በ5 ወር ውስጥ ብቻ ይቻሉና ራስዎን ይለውጡ
ከ ሰርተፍኬት ጋር ......
ለመመዝገብ ያናግሩን 👇
@MarkEngAcademy
☎️ 0908880599
❤ 12🔥 2
ናይጄሪያዊዉ ቢሊየነር አሊኮ ዳንጎቴ ከነዳጅ ተቆጣጣሪ አካል ጋር ግጭት ዉስጥ ገቡ
የናይጄሪያ ቁጥር አንድ ባለሀብት የሆኑት አሊኮ ዳንጎቴ እሁድ እለት ከነዳጅ ተቆጣጠሪ አካል ጋር ያለውን ውዝግብ ጋር ተባብሶ ቀጥሏል፡፡ በናይጄሪያ የሚገኙ የነዳጅ ማጣሪያዎችን አደጋ ላይ የሚጥል ርካሽ ነዳጅ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ አድርገዋል ሲሉ ዳንጎቴ ከተቆጣጣሪዉ አካል ጋር ያላቸዉን ልዩነት ገልጸዋል፡፡ናይጄሪያ በአፍሪካ ትልቁ የነዳጅ ዘይት አምራች ሀገር ብትሆን ከውጭ በሚገቡ ምርቶች ላይ ጥገኛ ናት፡፡ይህንኑ ችግር ለመቀየት የዳንጎቴ ነዳጅ ማጣሪያ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል።ዳንጎቴ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች ቁጥጥር ካልተደረገባቸው ለሥራ፣ ለኢንቨስትመንትና ለኢነርጂ ደህንነት ስጋት ይሆናሉ ብለዋል።
በሌጎስ በሚገኘዉ እና በቀን 650 ሺ በርሜል የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ ላይ ንግግር ያደረጉት ዳንጎቴ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች “የአገር ውስጥ አቅምን ለመፈተሽ” ጥቅም ላይ እየዋሉ ነው፣ ይህም ናይጄሪያ ወደ ኢንዱስትሪ ለምታደርገዉ ሽግግር ፈተና እየሆነ ይገኛል ብለዋል፡፡ዳንጎቴ የናይጄሪያ ሚድ ስትሪም እና ዳውንስትሪም ፔትሮሊየም ተቆጣጣሪ ባለስልጣን ኃላፊ ፋሩክ አህመድን በተመለከተ በዘርፉ ያላቸውን የአስተዳደር ስጋት እና የግል ወጪዎች ከህጋዊ ገቢ በላይ ናቸው በሚል ክስ ላይ ይፋዊ ምርመራ እንዲደረግ ጠይቀዋል።
አህመድ በሚመሩት ተቋማት ላይ ለቀረበዉ አስተያየት ወዲያውኑ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡ ነገር ግን ከዚህ ቀደም የዳንጎቴ ማጣሪያ በፔትሮሊየም ምርቶች ሽያጭ ላይ በብቸኝነት መያዝ እንደሚፈልግ ተናግረዉ ነበረ፡፡ የዳንጎቴ ነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካው ምርት የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ሊያሟላ አይችልም ሲሉ ተደምጠዋል።
Dagu
@Addis_News
@Addis_News
❤ 19🤪 4
ሊቃውንት አባቶቻችን ቤተክርስቲያን የሚለው ጥምር ቃል ሦስት ፍቺ እንዳለው ይገልጻሉ፡፡
የሚጀመሪያው ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የእያንዳንዳችን የክርስቲያኖች አካል እንደሆነ ይነገራል፡፡
ሦስተኛው ቤተክርስቲያን የክርስቲያኖች ሕብረት ነው፡፡
በሕብረት ውስጥ እኛነት እንጂ እኔነት ቦታ የለውም፣ በሕብረት ውስጥ ለእኛ እንጂ ለእኔ የሚለው ሀሳብ ውሃ አያነሳም፡፡ በዚህ ህብረት ውስጥ ክርስቲያኖች አንዱ ስለሌላኛው ድህነት ይጸልያል፤ ሌላኛው ስለሁሉም ደህንነት ይተጋል፡፡ ገንዘብ ያላቸው አቅመ ደካሞቹን ያግዛሉ፤ ጸጋው የበዛላቸው ደግሞ በጸሎትና በስግደት ስለሁሉም በእግዚአብሔር ፊት ይማጸናሉ፡፡
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምስራቅ በለሳ ወረዳ የሚገኘውን ታላቅ የበረከት ስፍራ ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳምን የልማት ሥራ እያገዝን ያለነው በዚሁ ክርስቲያናዊ አንድነት መነሻነት ነው፡፡
እኛ ቤተክርስቲያን ነን፡፡ አንዳችን ስለሁላችን የምንጸልይ፣ ሁላችን ስለሌሎቻችን ልማት የሚገደን፡፡
የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በረከት የተትረፈረፈልን ቤታችንን በእልልታ የሞላልን እኛ በክርስቶስ አንድ አካል ነንና በዚህ የጾም ወቅትም መልካም ስራዎቻችንን እናጠናክር።
ቪዲዮውን ያድምጡት፤ ይመልከቱት🙏
❤ 36
