ግጥም ብቻ 📘
Kanalga Telegram’da o‘tish
✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13 ✔ @wegoch @Words19 ✔ @seiloch @shiyach_bicha ✔ @zefenbicha @leul_mekonnen1
Ko'proq ko'rsatish65 859
Obunachilar
-2424 soatlar
-667 kunlar
-28630 kunlar
Postlar arxiv
Photo unavailableShow in Telegram
📍GHOST VOTE .
Ghost'ን vote እናድርግ
Ghosty’f sagalee kennaa
ጎስት'ነ ድምጺ ሃቡሉ
Ghost'ya keettidaa aayize
ጎስት vot አምሮዊ
Vote for Ghost
Vote por Ghost
投票给阿比伊,صوّتوا لأبيي
- ለጎስት ቮት ! 👇 🙏
https://www.tca2025.com/category/21
SHARE @getem
❤ 22👎 19😁 14
ከለታት ባንዱ ቀን
ህይወት ግቧን አውቀን
ኖረን ኖረን መጥቀን
በንባ ውዝፍ ስቀን
ከለታት ባንዱ ለት
ገፋንና ብረት
ቡጢ ተሰናዝረን በእጃችን ውጥረት
ግባችን ልንመታ ግብን አስተካክለን
አስቆጣሪ ጀግና በኛ ስም ወክለን
አክለን
በጥድፊያ
በልፊያ
ሰዓት አቀባብለን
ጊዜ ተቀባብለን
አንድ ሁኑ ስንባል ለየግል ተቆጥረን
ተዋደድን ብለን ካንገት ተወጣጥረን
ተመንጥረን
እንዳልሳቅን
አለቀስን
ፌዝ እንዳልያዝን በልባችን
ይበለን የታባታችን
ኖረን ኖረን መጥቀን
በንባ ውዝፍ ስቀን
አዙሮ
አዙሮ
ጊዜ ጣለን ከቀን።
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
❤ 31🔥 9👍 5🤩 1
ገና እሰክርሻለው
.................................
አለሜ ዞረብኝ
አለምሽን ጠጥቼ፣
አንቺን እንዳልሰክር
የሚያስቆም አጥቼ፤
አንቺን መንገዳገድ
አንቺን መፈራረጥ፣
ትቦው ስር ተኝቶ
ነፍስሽን ማዳመጥ፤
ሚያነሳኝም የለ ስሜ በአንቺ ጠፍቷል
ከአፋቸው ትችትን ብያኔን ለምዶታል!
.
#ተስፋን ቆራረጥኩት እብደቱ ተስማማኝ
#እምነትንም ጣልኩት ጤናን ስላስጠማኝ
#ፍቅርሽን ግን....
ልቤም ሊፍቅ ዳዳው
ውሳኔን አጣለት
ዘላለም ይመስል
ላይጠፋ ማለለት!
እንዴት አልስከርሽ
እንዴትስ አልጩህሽ
እንደሌላው አትፈርጂም
ዝም እኮ ነው መልስሽ!
ዝም..
ቁዝም...!
ጭጭ....
ረጭ....፣
ትዝታን አስታውሶ
ሰክሮ መነጫነጭ!
ሁከት...፣
ጩኸት....!
የውስጥን አፍኖ
ላይን ማሰቃየት!
(ገና እሰክርሻለው)
By @Weyblann
@getem
@getem
@getem
❤ 25👍 10🔥 4👎 2😢 2😁 1
ሁለቱም ይኑሩ!
(የሞገሴ ልጅ)
አለመተዋወቅ..
አለመቀራረብ..
አለመነጋገር..
አለመደራረብ፤
ዶግማ ይሁን እና-
ብዙ ይራራቁ፣
አይነፋፈቁ፣
አይተዋወቁ፤
አንድ አይሁኑ እንጂ-
ችግር እንዳይመጣ፣
ኁለቱም ይኑሩ፣
ዐይን’ና ሚጥሚጣ።
By @eyadermoges
@getem
@getem
@paappii
❤ 39👍 7🤩 4🔥 2😁 1
ሞልታ ለማትሞላ ለዚች ድንቡሎ አለም
መታገል ነው እንጂ መነፋረቅ የለም
ቻለው ችግርህን እጅ አትስጥ ለማንም
የደከምን ለታ ይብሳል ህመምም
ላገደመ ሁሉ ብሶትን አታውጋው
እራስህ ላንተ ኑር
ቃልን ውጠህ ዝጋው።
ቧልተኛ ነው ሁሉም
አይኑርህ አንድ ሰው
የሚገፋህ ካለ
ክንድህን አጉርሰው።
አርግፍለት ጥርሱን
አቅምሰው የጅን ጥም
"መታገል ነው እንጂ
መነፋረቅ የለም" ይላል ይሄ ግጥም።
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
❤ 62👍 18😱 7🔥 6🤩 5
ሰማሽ ወይ...
ያደለው ለሃገር - ጥይቱን ይጠጣል፣
ያላደለው ደግሞ - ቢራ ያማርጣል፤
ያገኘ ላምላኩ - እጁን ይዘረጋል፣
ተስፋ ያጣ ሃገር - ጥሎ ይጠረጋል፤
ታዳጊው ጎርምሶ - ለትዳር ይታጫል፣
ያመለጠው ኖሮ - በትላንት ይቆጫል፤
ኁሉም የየራሱን - እያነሳ ጣለው፣
ያንችን እና የኔን..........እኔስ ምን ልበለው?
By @eyadermoges
@getem
@getem
@getem
❤ 53👍 20🔥 8😱 4😢 4
ለምን ትመጫለሽ?
ወና መሆን ለምዷል
ባይተዋር ነው ሆዴ
ትራስ አቅፎ ማደር
ለምዶበታል ክንዴ።
ገላዬ ቀዝቅዟል
ልቤ ተሰቅዟል
እንስት ላለማመን
ዜሮ ነኝ ስተመን
ብትመጭም ከንቱ ነው
መመለስሽ ምንም
ስታወሪ አልስቅም
በእንባሽ አልቆዝምም
በድን ነኝ አልድንም ።
ለምን ትመጫለሽ?
የለሁም በድሮ
ሌላ ነኝ ዘንድሮ
ግዴ አይደለም ነገ
አትገርመኝም ጀንበር
ብራና ክረምቱ …
ቢዛወር ዓመቱ
ጨፍሬ አልደክርም
አልመታም አታሞ
ዓመት አንድ ቀን ነው
ለከሸፈ ታሞ ።
ለምን ትመጫለሽ ?
መምጣትሽ እንደ ቧልት
መመለስሽ ምንም ...
፡
ይህንን እያልኩኝ
ብናገር ብገጥምም
ስትመጪ ስዳበስ
በጣት በመዳፍሽ
ያልኩትን ዘንግቼ
አዲስ ሰው ሆንኩልሽ።
አትሄጂም አይደለ ?🙄
By (ሚካኤል አ)
@getem
@getem
@paappii
❤ 61😁 11👍 9🔥 5🤩 3
እኔ አንቺን ሳስታውስ
-------------------------
ወጪና ወራጁን
ተመልካቹን ቀርቶ
ቋንቋ ይምታታብኛል
ጠብቆ ይሁን ላልቶ
ብዙ ግዜ እንደሁም
ራሴን ረሳለው
እንዴት ተፈጠርኩኝ
ብዬ አወራለው
መሬት ጠፋች ብዬ
እዬዬ አስነካለው
መሬት ላይ ቁጭ ብዬ
መሬት ፈልጋለው
አንቺን ሳስብ ጊዜ ፤
"የመልኣክ ዝማሬ
ከሰማይ ሰማለው
ረቂቅ ነፍሳትን
መሬት ውስጥ አያለው"
አሁን በቀደም ለት
አንቺን ሳስብ ግዜ
እናት ወይ አባቴ
ብቻ ከሁለት አንዱ
ገፍትሬ አለፍኳቸው
በመንገድ ሲሄዱ
ፀሃዩን ከዝናብ
ገደሉን ከመንገድ
አሶችን ከኣዋፋት
አፈር ይሁን አመድ
ይሄን ሁሉ ነገር
በቃ ረሳለው
በሀሳብ በስብሼ
አንቺን ናፍቀለው
―――――
አንቺ እሱን ትያለሽ!
―――――
እልፍ አዕላፍ መንደር
ከሰማይ የራቀ
ከክዋክብት ግዛት
አልፎ የመጠቀ
ነፋሻማ ቦታ
ቆላ ያልሆነ ደጋ
ተከበን በእዋፋት
በአፅዋቶች መንጋ
እኔና አንቺን ብቻ
ቁጭ ብለን አያለው
በሃሳብ ዥዋዥዌ
ሄጄ ዳክራለው
―――――
እኔ አንችን ሳስታውስ!
―――――
በምናብ መዕበል
አብሬሽ ሄዳለው
አንቺን አወራለው
አንቺኑ አስባለው
እብሰለሰላለው
እኔነቴን ትቼ
አንቺ እኔን እላለው
―――――――
እናልሽ
―――――――
ባንቺ መውጣት መውረድ
ባልዘርፍ ምንም ቅኔ
ዘውድ ማረጌ
ሆነሽ ከምቶኚ የኔ
አንቺን ማስታወሱ
ስላሰጠኝ ደስታ
አልፈልግም መቼም
እንድትመጣ ሰምታ
እሷን ማሰብ ብቻ
ስላለው እርካታ
ስላገኘው እፎይታ
@getem
@getem
@paappii
❤ 73🔥 13👎 4
( እልፍ ሰላም )
============
ሲፈለግ የማይታጣ
ሲታሰብ የማይዘገይ
ታይቶ የማይሰወር
ሰጥቶ የማይታበይ
ማግኘት ማጣት ማይለውጠው
መሄድ መምጣት ማይቀይረው
በቅንጣት ጽድቅ ሚያሞጋግስ
ግዙፍ በደል የማይቆጥረው
ባዶነትን ማያናንቅ
መገፋትን ማይሰቀቅ
እርሱ ብቻ ተነጥሎ
ሁል ጊዜ የሚናፈቅ
የጎደፈን ማይጠየፍ
የሸሸውን ማይጥል ማይተው
ከወደደ እስከ ህይወት ጥግ
ይቅር ማለት ማይታክተው
መለያየት በሌለበት
በሱ ግዛት በሱ ዓለም
እልፍ ሰላም ካልሆን በቀር
ሞት ጥላቻ ክህደት የለም !!
By @kiyornad
@getem
@getem
@paappii
❤ 59🔥 3🤩 2
ያልወረደ እንባ
.
ላዩኝ ሁሉ ደስተኛ ነኝ እስቃለሁ፤
በነሱ ቤት መከፋትን የት አዉቃለሁ፤
.
የሚገርመዉ.....
በኔ መፍካት መቅናታቸዉ፤
እኔን መሆን ምኞታቸው፤
መች ያዉቁና ማስመሰሌን፤
የዉስጥ ሀዘን ስዉር ቁስሌን፤
በዉስጤ ታጭቆ ሰላም የሚነሳኝ፤
በነጋ በጠባ ሆድ ሆዴን ሚበላኝ፤
አዉጥቼ እንዳልጥለዉ አፍኖ የያዘኝ፤
ሳቅ የሸፋፈነዉ ያልወረደ እምባ አለኝ።
.......................................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤ 50👍 46🔥 11🤩 4😱 1
መሔጃ የለኝ !
ካይኖችሽ ብሸሽ ፥ ቅንድብሽ ስር ነኝ ።
ወዴትም ብዞር
ገላሽ ብቻ ነው ፥ የሚያዋስነኝ ።
ቅርቤም - ሩቄ
ኩነኔም - ጽድቄ
ከህጎች በልጦ ፥ ልብሽ የሚያዘኝ
አይንሽ ብቻውን ፥ የሚያናዝዘኝ
ያንቺው ታሳሪ ፥ ግዞተኛሽ ነኝ ።
ካንቺው ቀምቼ ፥ ላንቺ ምሰጥሽ
ከገዛ ራስሽ ፥ የማስበልጥሽ
ምንም ቢሰማኝ ፥ የማላመልጥሽ
ወስልቼ ብሄድ ፥ ከገላሽ ምሕዋር
ተኝቼ ምገኝ ፥ ከትዝታሽ ጋር
ወዲህም ሳራ ፥ ወዲህም አጋር !
ካንቺ ጋር መሮኝ
ሌላ ሴት አምሮኝ
ጥዬሽ ለመሄድ ፥ አስር ብወራጭ
አንቺን ነው ማገኝ ፥ ልክ እንደ አማራጭ ።
By Habtamu Hadera
@getem
@getem
@paappii
❤ 32👍 1
ያልታደልኩት እኔ
አይንሽ እርቆብኝ ሰርክ ብንገላታም
ወንድ ልጅ ነኝና ተስፋዬን አልፈታም
የሚመሩን ሁሉ መምሪያ ሰነዳቸው
ምን ቢሆን አንድነት
በሬሳ አካላች ቄጤማ ነስንሰው ሰሩልን ሰገነት
ሰብከውን በኪዳን
ሰብከው በመንግስቱ
ተደመርን ብለው ምን ቢያጎበድዱ
የጀርባ ላይ እከክ ሆኑ አንዱ ጎሳ ላንዱ
በመስኮት በመስኩ ምንስ አሸብርቀው ፍቅር ፍቅር ቢሉ
እያቸው አለሜ
ጩቤ ተጨባብጠው ሰላም ሲባባሉ
ያልታደልኩት እኔ
አይንሽ እርቆብኝ ሰርክ ብንገላታም
ወንድ ልጅ ነኝና ተስፋዬን አልፈታም
አዲስ ኪዳን ቢፈለሰፍ
አዲስ መንግስት ቢዋቀርም
ዱር ጫካ ገብቼ ሳላይሽ አልቀርም
የፈለገ ቢሆን ሰላም ለአደባባይ ለመንደሩ
ለሀገርህ ዝመት ብለው ገበሬን ነው ሚገብሩ
ሰርክ አራሽ መሬቱን
ሰርክ ቀዳሽ ታቦቱን
ነፍጠኛ ተኳሹን
ሀገር ሲሉት የሚነሳን
ወገን ሲሉት አለሁ የሚል
ምን ቢጨቆን አፉን ይዞ ትቅደም ባለ አንድ ሀገሩን
ሜዳ ላይ አጠፉት
ኪዳን ፍቅሩን ጥለው ሰበሩት ማገሩን
ያልታደልኩት እኔ
አይንሽ እርቆብኝ ሰርክ ብንገላታም
ወንድ ልጅ ነኝና ተስፋዬን አልፈታም
አለሜ
አይንሽን ባላይም ቃልኪዳን አልፈታም
ሁሌ እወድሻለሁ
ሚያገናኘን መንግስት እስኪመጣ ድረስ
እናውርድ እላለሁ
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
❤ 31🔥 4
ያላንቺ ይቅርብኝ!
(የሞገሴ ልጅ)
ዐየሽ የኔ ናፍቆት-
ካንቺ በፊት እኔ - ኖሬአለሁ ለናቴ፣
ቆንጥጣ አባራኝ - በሚናፈቅ ቤቴ።
ያኔ ግን - ልጅነት-
ከጎኔ ስትለይ - ናፍቆት ቢቀጣኝም፣
አቅፋኝ እየተኛች፣
በናፍቆቷ መራብ - - ጭራሽ አያውቀኝም።
ጭራሽ አደግ ስል...
እሷን መውደድ ሳልተው - አንቺን በልብ ይዤ፣
አጠገቤ ሆነሽ፣
ናፍቆትሽን ፃፍኩት - ማግኘቴን ሰርዤ።
እንደው ግን የምልሽ?
እለት እለት ጾሜ፣
ያለኝን መፅውቼ፣
ከገነት ለመግባት - የምጠባበቀው፣
ካንቺ ጋራ ስሆን፣
ከሚሰማኝ ምቾት - እንዴት ነው ሚልቀው?
እንጃ ያሳስባል-
ካንቺ በላይ ናፍቆት የሚያስይዝ ቢመጣ፣
ከሆነ ነው እንጂ፣
አንችው ሰማይ ሆነሽ - ልቤ በልብሽ ላይ ገነት ተቀምጣ።
በዛ አትበይ እንጂ...
ካንቺ ተለይቶ - መኖር የሳት ባሕር፣
ካንቺጋራ ሆኖ - ሲኦል መግባት ክብር፣
ከነ’ንትንሽ መሳም - የዘላለም እረፍት፣
ማፍቀርሽን መግፋት - ኦሜጋ ስህተት፣
አንችን አለማሰብ - የድርቀትም አያት፣
ፈልጎሽ መኳተን - የክብር ኁሉ አናት፤
ይመስለኛል እኔ.....
ለገነት ለሲኦል - አንቺ ነሽ ሚዛኔ፣
ጨርሼ መጽደቄ - ወይም መኮነኔ፣
ፈዋሿ መስቀሌም - ገዳዩዋ መብረቄ፣
የሰማዩን እማ.........አልተወለድኩኝም በፅንፀት አውቄ።
By @eyadermoges
@getem
@getem
@getem
❤ 30🔥 5👎 1
•
የመንገዴ ፍጻሜ ነሽ
ከአድማስ የአድማስ መጨረሻ
የሀሰሳዬ ፍጻሜ የጉዞዬ መዳረሻ
✻‧
ባለፈው ወይኔ ጎድሎ
እቸረው (እሰጠው) ቢያጥረኝ
ማርያምን መስለሻት መጣሽ
በምልጃሽ ምልአትን ቸረኝ
"አይሆንም" ያልኩት ሆነልኝ
አያልፍም ያልኩት አለፈ
"ከበደኝ ታከተኝ" ያልኩት በፍቅርሽ እየታቀፈ ።
✻‧
ነውሬን አንቺው ሸፈንሽው
ጋረድሽው የሀፍረት ታሪኬን
የህይወት ማይ እየሆንሽኝ
አነጻው እድፋም መልኬን
ወደድኩሽ እስከ ጥ • ግ • ጥ • ጉ
ለፍቅርሽ ነፍሴን አስገዛሁ
አንድ ሆኜ መኖር ያቃተኝ
ዕልፍ ሆኜ በፍቅርሽ በ • ዛ • ሁ ።
#የአብስራ_ሳሙኤል
@YabisraSamuel
@getem
@getem
@getem
❤ 38👍 4
