ru
Feedback
አዲስ ነገር መረጃ

አዲስ ነገር መረጃ

Открыть в Telegram

#አዲስ_ነገር_መረጃ #መረጃዎች_በትኩሱ ና ሳይዉሉ እንዲሁም ሳያድሩ በቻናሉ በኩል ይደርሳሉ Addis Ababa , Ethiopia Buy Ads : https://telega.io/?r=UbutLo2z #ለአስተያየት እና ለማስታወቂያ ስራዎች 👇👇 @Addisnegermereja_bot

Больше
103 397
Подписчики
-6824 часа
-937 дней
+16730 день
Архив постов
00:53
Видео недоступноПоказать в Telegram
19.45 MB
2
Фото недоступноПоказать в Telegram
የኢንተርኔት ንግድን ወደ ግብር‼ ገቢዎች ቢሮ የኢንተርኔት ንግድን ወደ ግብር ሥርዓቱ የሚያስገባ አሠራር መዘርጋቱን አስታወቀ : በአዲስ አበባ ከተማ ግብር የማይሰበሰብበት የኢንተርኔት (ኦንላይን) ንግድ እየተስፋፋ በመሆኑ ዘርፉን ወደ ግብር ሥርዓት ለማስገባት የሚያስችል አሠራር መዘርጋቱን የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ገለጸ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ፣ የማኅበራዊ ሚዲያው እየፈጠረ ባለው ተፅዕኖ የተነሳ፣ በአሁኑ ወቅት የኦንላይን ንግድ በከተማ እየተስፋፋ መሆኑን፣ ከፍተኛ የግብይት እንቅስቃሴ የሚከናወንበትና ሰፊ የገንዘብ ዝውውር የሚደረግበት እየሆነ መምጣቱን፣ ነገር ግን ቁጥሩ ይኼ ነው ብሎ ለመናገርና ምን ያህል ግብር አሳጥቷል የሚለውን ለማወቅ ጥናት ማድረግ እንደሚጠይቅ ተናግረዋል። @Addis_News @Addis_News
Показать все...
🤪 22 16🤔 5🤣 3👍 1💯 1😨 1
ኢሳያስ ካሳ (ዶ/ር ) የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት በመሆን ሲሾሙ፡፡ መንግስታዊው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ኢሳያስ ካሳ (ዶ/ር) የባንኩ ፕሬዝዳንት ሆነው መሾማቸውን አስታወቀ። የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ኢሳያስ ካሳ (ዶ/ር ) ለአንድ ዓመት የባንኩ ፕሬዝዳንት በነበሩት እመቤት መለሰ (ዶ/ር) ምትክ ተሾመዋል። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሰራተኞች የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ በመሆን መሾማቸውን ባንኩ ገልጿል። የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በቦርድ አባልነት ደግሞ ሶፍያ ካሳ (ዶ/ር)፣ ስዩም መኮንን፣ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር)፣ አቶ ሃቢብ መሀመድ፣ ረዳት ፕሮፌሰር ማርታ በለጠ እና ጥላሁን እስማኤል (ዶ/ር) መመረጣቸውን በመግለጽ ለሁሉም ተሿሚዎች መልካም የስራ ዘመን ተመኝቷል። ባንኩን ለአራት ዓመታት በፕሬዚዳንትነት የመሩት ዮሐንስ አያለዉ ( ዶ/ር) በግል ምክንያት ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸውን ተከትሎ ዶ/ር እመቤት መለሰ ከጥቅምት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ፕሬዝዳንት ሆነዉ ሲያገለግሉ ቆይተዋል። @Addis_News @Addis_News
Показать все...
19
እናት እና ልጅ ምሳ ከበሉ በኋላ ለጊዜው ባልታወቀ  ምክንያት  በተከታታይ ሰዓት ሕይወታቸው አለፈ   👉 ፖሊስ  የአሟሟታቸውን ሑኔታ በጥልቅ እየመረመረ ይገኛል እንደ ምስራቅ ሐረርጌ ዞን ፖሊስ ዋና መምርያ የኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ካስዬ አበበ ገለፃ እናት እና ልጅ ምሳ ከበሉ በኋላ በተከታታይ ሕይወታቸው ማለፉን ተናግረዋል፡፡   እናት እና ልጅ ታህሣስ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ አምስት ሰዓት ተኩል መስጊድ ሰላት ቆይተው ወደቤታቸው ገብተው ምሳቸውን ከበሉ በኋላ እናት ሻወር ለመውሰድ ሻወር ቤት ሲደርሱ አረፋ በመድፈቅ እና በመወራጨት ሲወድቁ የተመለከተች ልጅ በድንጋጤ በመጮህ የአካባቢው ሠው ሲደርስ ህይወታቸው ማለፉ ተረጋግጥዋል ሲሉ ተናግረዋል። ከሰዓት ቆይታ በኃላም ልጅ እንደ እናቷ ከአፏ አረፋ በመድፈቅ ስትወድቅ ወደ ካራሚሌ ሆስፒታል ለህክምና ብትላክም በህክምና ላይ እያለች ህይወቷ አልፏል።ፖሊስ የሟቾችን አስክሬን ለምርመራ ወደ አዲስ አበባ ዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል የላከ ሲሆን በተጨማሪ ለምሳ የተመገቡትን ምግብ እና የጠጡትን ውሀ ናሙና ለኢትዮጵያ ምግብና መድሐኒት ቁጥጥር ባለ ስልጣን በመላክ ስለ አሟሟታቸው ምክንያት ሰፊና ጥልቅ ምርመራ እያደረገ መሆኑን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል፡፡ @Addis_News @Addis_News
Показать все...
😢 38 16💔 5👍 2
በንግድ ባንኮች መካከል ያለው የዶላር መግዣ ዋጋ ልዩነት እስከ 15 ብር ከፍ አለ ኢትዮጵያ ወደ ገበያ ተኮር የምንዛሪ ተመን ሥርዓት ከተሸጋገረች ከአንድ ዓመት በኋላ፣ የአገር ውስጥ የውጭ ምንዛሪ ገበያ በአስደንጋጭ ሁኔታ መከፋፈሉንና የግብይት ወጪዎች በእጅጉ መጨመራቸውን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማኅበር ገለጸ። የንግድ ባንኮች ለአንድ የአሜሪካ ዶላር የሚገዙበትና የሚሸጡበት ተመን ላይ ያለው ልዩነት እስከ 15 ብር ድረስ ከፍ ማለቱ፣ በገበያው ውስጥ ጤናማ ውድድር እና የተቀናጀ አሠራር አለመኖሩን የሚያመላክት ትልቅ ፈተና እንደሆነ ተገልጿል። የኢኮኖሚክስ ማኅበሩ ባወጣው ሪፖርት መሠረት በ2018 የበጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ብር ከአሜሪካ ዶላር አንፃር በ8.1 በመቶ በማሽቆልቆል ከ135.5 ወደ 146.4 ብር ደርሷል፤ በታኅሣሥ 2018 ዓ.ም ደግሞ ከ154 ብር በላይ ሆኗል። እንደ ሪፖርቱ ከሆነ በባንኮች የመግዣና የመሸጫ ዋጋዎች መካከል ያለው ልዩነት ባለፈው ሩብ ዓመት ከ3.1% ወደ 6.8% የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ከፍ ብሏል። ይህ መስፋፋት የዘርፉ ተዋናዮች አደጋን የመፍራት ዝንባሌ፣ የተገደበ የባንኮች መካከል የንግድ ልውውጥ እና መሰረታዊ የገበያ ውዝግብ መጨመሩን የሚያመለክት መሆኑ ተጠቁሟል። @Addis_News @Addis_News
Показать все...
13😢 4
Фото недоступноПоказать в Telegram
96 በመቶ የሚሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ከሚገባው በላይ ጨው ይጠቀማል ተባለ፡፡ በጨው ውስጥ የሚገኘው ንጥረ ነገር ሶዲየም የሰውነትን የፈሳሽ ሚዛን ለመጠበቅ እንዲሁም ኦክስጅንና ንጥረ ነገሮችን ለማጓጓዝ አስፈላጊ ቢሆንም በርካታ ዜጎች ከሚመከረው በላይ ጨው እንደሚጠቀሙ ተነግሯል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስነ ምግብ ህክምና ባለሙያ ረዳት ፕሮፌሰር ዘላለም ደበበ ለብስራት ሬድዮ እንደተናገሩት አንድ አዋቂ ሰው በቀን ከአምስት ግራም የማይበልጥ ጨው መመገብ ይኖርበታል። ነገር ግን በኢትዮጵያ 96 በመቶ የሚሆነው የህብረተሰብ ክፍል ከሚገባው በላይ ጨውን ይመገባሉ ብለዋል። ይህም የጤና መታወክን እንደሚያስከትል ረዳት ፕሮፌሰር ዘላለም ገልፀው በተለይም ደግሞ ለደም ግፊት ህመም፣ ለጨጓራ ካንሰር፣ ለስትሮክ እንዲሁም ለልብ ድካምና ተያያዥ በሽታዎች ሊያጋልጥ እንደሚችል ጠቁመዋል። ቅጠላ ቅጠሎችንና ቅመሞችን በመጠቀም ሰዎች የሚያበስሉትን ምግብ ማጣፈጥ ሲገባቸው ከሚመከረው በላይ ጨውን ይመገባሉ። እንደዚሁም በአብዛኛው ምግብ ውስጥ ጨው የሚገኝ መሆኑን የስነምግብ ህክምና ባለሙያዋ ተናግረው ጤናን በአግባቡ ለመጠበቅ በልኩ መጠቀም እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል። @Addis_News @Addis_News
Показать все...
18🤪 4🤔 2😍 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
በኢትዮጵያ ፈቃድ ተሰጥቷቸው ሲሰሩ የቆዩ የሁሉም የስፖርት ውድድር ውርርድ ድርጅቶች የሥራ ፈቃድ ተሰረዘ የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ሁሉንም የስፖርት ውድድር ውርርድ ድርጅቶች የሥራ ፈቃዶች ከታህሳስ 06 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ መሰረዛቸውን ገልፇል። የፈቃድ ስረዛው በውርርድ እና በፋይናንስ ዘርፉ ላይ በተካሄደ አገር አቀፍ ጥልቅ ግምገማ ላይ ተመስርቶ የሕዝብን ጥቅም ለማስከበር የተወሰደ እርምጃ መሆኑን ድርጅቱ ገልፇል። ውሳኔው በስራ ላይ ባሉትና ቀደም ሲል በይፋ በታገዱት በሁሉም የውርርድ ድርጅቶች በእኩልነት ተፈጻሚ ይሆናል ተብሏል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በሂደት ላይ ያለው ምርመራ በዘርፉ ውስጥ የተንሰራፋ ሀገ-ወጥ አሰራር፣ የፈቃድ ውል ጥሰት እና ለብሔራዊ ደህንነት ስጋት የሚሆኑ ህገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውሮች እንዳሉ በግልጽ አመላክቷል። ለስፖርት ውርርድ ድርጅቶች እና ሲስተም ኦፕሬተሮች/አቅራቢዎች ከታሀሳስ 06 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአካል፣ በዲጂታል ወይም በሌላ መንገድ የሚካሄድ ማንኛውንም የውርርድ ሥራ እንዲያቋርጡ ትዕዛዝ ተሰጥቷል። ሁሉም የገንዘብ ማስገቢያ መንገዶች አገልግሎት መስጠት እንዲያቆሙም ታዟል። አዲስ ውርርድ መቀበል ፈጽሞ አይቻልም ተብሏል።። @Addis_Reporter @Addis_Reporter
Показать все...
28👏 7🫡 2
Фото недоступноПоказать в Telegram
በአፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ የተመራ የ ኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን የኢራንን የመከላከያ ስኬቶች ማሳያ ጎበኘ! በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በቴህራን የኢራንን የመከላከያ ኢንዱስትሪ ስኬቶችን የሚያሳይ ኤግዚቢሽን ጎብኝቷል። ጉብኝቱ ከከፍተኛ የኢራን ባለስልጣናት ጋር የተደረገውን ስብሰባ ተከትሎ የመጣ ሲሆን ልዑካን ቡድኑ ትናንት እሑድ በኢራን መከላከያ ሚኒስቴር ውስጥ በሚገኘው የሀገሪቱ የመከላከያ ኢንዱስትሪ ስኬቶች ላይ ያተኮረውን ኤግዚብሽን ተዘዋውሮ መጎብኘቱ ተጠቁሟል። የኢትዮጵያ ፓርላማ አባላት ወደ ቴህራን የተጓዙት በኢራን ፓርላማ አፈ-ጉባኤ ሞሃመድ ባገር ጋሊባፍ ይፋዊ ግብዣ ነው። በጉብኝቱ ወቅት፣ ልዑካን ቡድኑ በኢራን የመከላከያ ዘርፍ ስላሉት የቅርብ ጊዜ ዕድገቶች ማብራሪያ የቀረበለት ሲሆን፣ በኢራን ባለሙያዎችና ኢንዱስትሪዎች የተመረቱ የተለያዩ ወታደራዊ መሣሪያዎችን ተመልክቷል። በጉብኝቱ ላይ ከተገኙ ባለስልጣናት መካከል የፍትህ ስርዓት ኃላፊ ግሆላም-ሆሴይን ሞህሰኒ ኤጄይ፣ ፕሬዝዳንት መስኡድ ፔዜሽኪያን እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ይገኙበታል ሲል የኢራኑ መህር የዜና ወኪል ዘግቧል። @YeneTube @FikerAssefa
Показать все...
22🤔 9🤪 6🫡 4👍 3😢 2
ሐሞት ጠጠር የሚያስከትሉ 5 ዋና ዋና ምክንያቶችን ይወቁ ​የሐሞት ጠጠሮች ብዙውን ጊዜ ያለ ምንም ምልክት ይፈጠራሉ። ነገር ግን፣ ጠጠሮቹ በሐሞት ቱቦ ውስጥ ከተጣበቁ፣ ከባድ ህመም፣ ማስመለስና የምግብ አለመፈጨት ችግሮችን ሊያስከትሉ ይችላሉ። የህክምና ባለሙያዎች እንደሚናገሩት አንዳንድ የተሳሳቱ የአመጋገብ እና የአኗኗር ዘይቤ ልማዶች ሳያውቁ የሐሞት ጠጠር ተጋላጭነትን ሊጨምሩ ይችላሉ። ሀኪሞች ብዙውን ጊዜ ለዚህ ምክንያት ነው የሚሏቸውን  አምስቱ  ልማዶች አሉ። ​ በጊዜው ካልታከመ፣ የላፓሮስኮፒክ ቀዶ ጥገናም ሊያስፈልግ ይችላል። የሐሞት ጠጠር ተጋላጭነትን የሚጨምሩትን ልማዶች እንመልከት። ​1. በአግባቡ አለመመገብ አንዳንዴ ​ምግብን መመገብ  መዝለል ሐሞት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በሐሞት ከረጢት ውስጥ እንዲከማች ሊያደርግ ይችላል። ኮሌስትሮል በቆመ ሐሞት ውስጥ በቀላሉ ሊከማች እና ጠጠሮችን ሊፈጥር ይችላል። ስለዚህ፣ በየጊዜው እና በሰዓቱ መመገብ አስፈላጊ ነው። ​2. ከመጠን በላይ የተጠበሱ ወይም የሰባ ምግቦችን መመገብ ​የተጠበሱ እና ጤናማ ያልሆኑ ቅባቶች እንዲሁም የተቀነባበሩ ካርቦሃይድሬቶች በሐሞት ውስጥ ያለውን የኮሌስትሮል መጠን ይጨምራሉ። እነዚህን ምግቦች ለረጅም ጊዜ መመገብ ለሐሞት ጠጠር ተጋላጭነትን የሚጨምር ሲሆን በኋላ ላይ ቀዶ ጥገና ሊያስፈልግ ይችላል። ​3.  ብዙ እንቅስቃሴ የማያደርግ የአኗኗር ዘይቤ ​የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማጣት የሰውነት ሜታቦሊዝምን ያዘገየዋል እና የሐሞትን ፍሰት ይቀንሳል። ውፍረት ለሐሞት ጠጠር ዋነኛ መንስኤዎች አንዱ ነው። መደበኛ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና ክብደት መቆጣጠር ከዚህ ይከላከላሉ። ​4. በፍጥነት ክብደት መቀነስ ወይም ድንገተኛ አመጋገብ (crash dieting) ​ድንገተኛ እና ፈጣን ክብደት መቀነስ ጉበት ከመጠን በላይ ኮሌስትሮል እንዲያመርት ሊያደርግ ይችላል፣ ይህም ሐሞት እንዲረጋጋና ለጠጠር መፈጠር ተጋላጭነትን እንዲጨምር ያደርጋል። ስለዚህ ክብደትን በዝግታ እና በአስተማማኝ ሁኔታ መቀነስ የተሻለ ነው። ​5. በአመጋገብ ውስጥ የፋይበር እና የውሃ እጥረት ​አነስተኛ ፋይበር እና ውሃ መመገብ የምግብ መፈጨትን ሊያዳክም እና የሐሞት ፍሰትን ሊቀንስ ይችላል። ፍራፍሬዎች፣ አትክልቶች እና ሙሉ እህሎች ጠጠሮችን ለመከላከል ይረዳሉ። በቂ ውሃ መጠጣት ሐሞት ፈሳሽ እንዲሆን ያደርጋል እና ተጋላጭነትን ይቀንሳል። ​ቀዶ ጥገና መቼ አስፈላጊ ይሆናል? ​ሁሉም የሐሞት ጠጠሮች ሕክምና አያስፈልጋቸውም። ነገር ግን ተደጋጋሚ ህመም፣ ኢንፌክሽን፣ የፓንክሬአስ እብጠት  ወይም የሐሞት ቱቦ መዘጋት የሚያስከትሉ ከሆነ፣ ባለሙያዎች ላፓሮስኮፒክ ሐሞት ማስወገድ (laparoscopic cholecystectomy) በጣም አስተማማኝ መፍትሄ እንደሆነ ያምናሉ። ውስብስብ በሆኑ ሁኔታዎች ውስጥ ደግሞ ክፍት ቀዶ ጥገናም ሊያስፈልግ ይችላል። ​ሚዛናዊ አመጋገብ፣ መደበኛ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ፣ በቂ ውሃ መጠጣት እና ድንገተኛ አመጋገብን ማስወገድ የመሳሰሉ ልማዶች የሐሞት ጠጠር ተጋላጭነትን በእጅጉ ሊቀንሱ ይችላሉ። ለረጅም ጊዜ የሚቆይ የሆድ ህመም ወይም የምግብ አለመፈጨት ችግር ካለብዎ፣ ወዲያውኑ የሕክምና ምክር መፈለግ አለብዎት—ይህ ውስብስቦችን ይቀንሳል እና በአብዛኛው የአስቸኳይ ጊዜ ቀዶ ጥገናን አስፈላጊነት ያስወግዳል። @Addis_News @Addis_News
Показать все...
40💯 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
በኮሎምቢያ የትምህርት ቤት አውቶቡስ ገደል  ገብቶ 17 ሰዎች ሞቱ ​ 20 ሰዎች ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል። አውቶቡሱ  40 ሜትር ጥልቀት ወዳለው ገደል ነበር የገባው። አደጋው የደረሰው ትናንት ሲሆን አውቶቡሱ ​የአንቲዮኬኖ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን  ከቶሉ  ወደ ሜደሊን እየወሰደ  ነበር። ተማሪዎቹ የምረቃ በዓላቸውን ከባህር ዳርቻ አክብረው ሲመለሱ ነበር አደጋው የደረሰው። በሰሜን ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍል  በደረሰው አደጋ  16 ተማሪዎችና የአውቶቡሱ ሹፌር እንደሞቱ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ​የአንቲዮኪያ  ክልል ገዢ የሆኑት አናድሬስ ጁሊያን ሬንዶን የአደጋው መንስኤ በምርመራ ላይ መሆኑን ለመገናኛ ብዙኃን ተናግረዋል። ​ሬንዶን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ባሰፈሩት ቪዲዮ ላይ፣ ከአደጋው የተረፈች አንዲት ተማሪ “እኔ ተኝቼ ነበርኩኝ፣ በድንገት ጩኸት ሰማሁ፣ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ምንም የማስታውሰው ነገር የለም” ስትል ተናግራለች። ​ተማሪዎቹ ምረቃቸውን ለማክበር ውብ የሆኑትን የካሪቢያን የባህር ዳርቻ ከተሞችን ቶሉ እና ኮቬናስን  ጎብኝተው ነበር። የነፍስ አድን ሰራተኞች በስቴቸር  በመጠቀም በሕይወት የተረፉትን ከገደል ውስጥ አውጥተዋል። ​ፕሬዝዳንት ጉስታቮ ፔትሮ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ባሰፈሩት መልዕክት ለተጎጂ ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝተዋል። Fidel post @Addis_News @Addis_News
Показать все...
😢 23 15👏 1
ከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ ንጉሡ መልኳ ውብ የሆነች ብላቴና ሊያገባ ወዶ መልእክተኞችን መርጠው ያመጡለት ዘንድ ላከ። እነርሱም መላ ሀገሪቱን ሲያስሱ ቆይተው ሮሜ ውስጥ ባለ አንድ ገዳም ውስጥ ከሌሎች ደናግል ጋር ያገኟትን ቅድስት አርሴማ ሲያገኙ ሥዕሏን ስለው ለንጉሡ ላኩለት። እናታችን ራሷን የክርስቶስ ሙሽራ አድርጋ የለየች የፊቷ መልክ እጅግ ልዩ፣ ደምግባቷ ያማረ ነበረች። ንጉሡም ይህን ሥዕል እንዳየ እጅግ ወደዳትና እንዲያመጡለትም አዘዘ። ደናግልኑ ይህን እንደሰሙ ከቅድስት አርሴማና ከገዳሙ እመምኔት ቅድስት አጋታ ጋር ሸሽተው ወደ አርማንያ ሄዱ። አካባቢው ንጉሥ ድርጣድስ የሚገዛው ነበርና ከንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ መልእክት ደርሶት ሲያስፈልጋት ከደናግሉ ጋራ አገኛቸው። እርሱም በውበቷ በእጅጉ ተስቦ ይህችን ውብ ሴትማ ለራስ ነው እንጂ ለሌላ አሳልፎ መስጠት አይገባም ለራሱ ፈልጎ እዚያው አኖራት። ከደናግሉም ጋራ ካሠራቸው በኋላ እናታችን ቅድስት አርሴማን በብዙ ሊያታልላት ሞከረ። እርሷ ግን በመንፈሳዊ ሕይወቷ ፍጹም ራሷን አሳልፋ የሰጠች፣ ራሷንም ለቸሩ አምላካችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ሙሽራ ያደረገች ናትና ለሰማያዊ ሙሽርነቷ የታመነች ሆነች። ንጉሡም ደጋግሞ ቢሞክር አልሆንለት አለ። በኋላም እመ ምኔቷን እንድታባብላት ላካት፤ እመ ምኔቷ ግን “አይዞሽ! እንዲህ ላለው ምድራዊ ኃላፊ ነገር እንዳትታለይ፤ ሰማያዊ ሙሽርነትሽንና ንጽሕናሽን አጽኚ” ብላ ይበልጥ አጸናቻት። ንጉሡም በግድ ይዟት ሊሄድ ቢል ኃይለ መንፈስ ቅዱስ አድሮባት ነበርና ያንን በጦር የጎለመሰ ሰውነት ያለውን ብርቱ ጦረኛ ከመሬት ፈጠፈጠችው። ንጉሡም አንዲት ትንሽ ወጣት እንደምን ጣለችኝ ብሎ እጅግ አፈረ። እጅግም ተቆጥቶ ቅድስት አርሴማን ሥቃይዋን ሊያበዛባት ተነሳ እርሷንም በደናግሉ ሁሉ ፊት አሠራትና በፊቷ አንድ በአንድ አንገታቸውን ቀላቸው። እርሷ ግን “አይዟችሁ!” እያለች ታጽናናቸው ነበር። ይልቁንም ትሳቀቃለች ብሎ ባደረገው ነገር ቅዱሳኑ ሰማያዊ አክሊልን ሲቀበሉ ትመለከት ነበር። ይህን ሲጨርስም “አንቺን እንደሌሎቹ ቶሎ አልገድልሽም” ብሎ በብዙ መከራ እጅግ አሠቃያት። በመጀመሪያ ሁለቱን ጡቶቿን ቆረጠ፤ ቀጥሎም ሁለቱን ዐይኖቿን አወጣቸው፤ እርሷም እንዲህ ሳለች ንጽሕት ድንግል እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልዩ የብርሃን ዐይኖችን ሰጠቻት። በመጨረሻም እርሷን ማሠቃየት ሲሰለች ከቀሩት ከሰባ አምስት ወንዶችና ከሃያ ሰባት ደናግል ሴቶች ጋራ መስከረም ሃያ ዘጠኝ ቀን አንገቷን ሰየፋቸውና የሰማዕትነትን የድል አክሊል ተቀዳጁ። ታኅሣስ 6 ቀንም የቅድስቲቱ ሰማዕት ቤተክርስትያኗ የከበረችበትና አብረዋት ከተጋደሉ 27 ደናግላን ጋር ሥጋቸው የፈለሰበት ነው። ቅድስት አርሴማ ከሃያ ሰባቱ ደናግል ጋራ ሰማዕትነት ከተቀበለች በኋላ ንጉሡ ድርጣድስ ፈጽሞ ታመመ ታወከም። በትውፊት ታላቅ ወንድሟ እንደኾነ የሚነገርለት ቅዱስ ጎርጎርዮስ ሊቀ ጳጳሳትን አስቀድሞ አሥሮት ነበር። በኋላም ቅዱስ ጎርጎርዮስን ፈታውና ከደዌው ዳነ፤ የቅዱሳን ደናግልና የቅድስት አርሴማንም የቅዱሳን ሰማዕታቱን ዐፅመ ፍልሠታቸው ታኅሣሥ ስድስት ቀን በቅዱስ ጎርጎርዮስ ተደረገ፡፡ እንዲሁ ደግሞ የእርሷ ማኅበርተኞች የሚባሉ የመቶ ዐሥራ ዘጠኝ ሰማዕታት ዝክራቸው ነው። በስሟ ያማረ ቤተ ክርስቲያን ሠርተው አከበሩበት። ቅድስት አርሴማ በሰማዕትነት ስታርፍ ጌታችን ነፍሷን በክብር ተቀበላት ራሷን ለእርሱ በሙሽርነት አሳልፋ ሰጥታለችና ብዙ ቃል ኪዳንም ሰጣት፡፡ በቃል ኪዳኗ የታመኑ ገዳማውያን ዘወትር አማልጂን ይሏታል፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና ከበረከታቸው እንሳተፋለን፡፡ ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ 1000442598391 ወይም አቢሲኒያ ባንክ 141029444 ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
Показать все...
43🤣 2
Фото недоступноПоказать в Telegram
18
Фото недоступноПоказать в Telegram
. በሌሎች ሰወች ፖስት የተደረጉ ያገለገሉ እቃዎችን ፎቶ ፣ አድራሻ ፣ ዋጋ እና የእቃውን ባለቤት ስልክ ቁጥር በ ET Creatives በቀላሉ ያገኛሉ ✅ JOIN 👉 https://t.me/ET_Creatives_Family ET Creatives
Показать все...
6
Фото недоступноПоказать в Telegram
ይሸጣል ብሎ መለጠፍ ድሮ ቀረ ያገለገለ እቃዎትን ባሉበት ፎቶ በማንሳት ይሽጡ - መግዛትም ይቻላል ✅ ልብ ይበሉ ሁላችንም ቤት አንድ የማንፈልገውና የማንጠቀምበት ያገለገለ እቃ አለ በተቃራኒው ደግሞ ያንን እቃ የሚፈልጉ ግን የት እንደሚገኝ የማያውቁ ሰዎች አሉ። አላማችን እርሶ የማይጠቀሙበትን ያገለገለ እቃ በቀላሉ ካሉበት ሆነው ፖስት በማስደረግ እንዲሸጡ ማስቻል ሲሆን ያገለገለ እቃ መግዛት ሲፈልጉ ደግሞ በቀጥታ ከእቃው ባለቤት በጥሩ ዋጋ እንዲገዙ ማገዝ ነው። ስለሆነም እርሶም ቤት አገልግሎት ሳይሰጥ ቦታ ይዞ የተቀመጠ ያገለገለ እቃ ካሎት ፎቶ አንስተው ይላኩልን ወይም በሌሎች ሰወች ፖስት የተደረጉ ያገለገሉ እቃዎችን ፎቶ ፣ አድራሻ ፣ ዋጋ እና የእቃውን ባለቤት ስልክ ቁጥር በ ET Creatives በቀላሉ ያገኛሉ ✅ JOIN 👉 https://t.me/ET_Creatives_Family ET Creatives
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
ትራኦሬ ዊግ ከለከሉ‼️ የቡርኪናፋሶው መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ ከውጪ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ አርቲፊሻል ጸጉር (በተለምዶ ዊግ በመባል የሚታወቁት) ወደ አገራቸው ቡርኪና-ፋሶ እንዳይገቡ ከልክለዋል። አፍሪካ አህጉር እንጂ "ሙዚየም አይደለችም" ብለዋል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter
Показать все...
👍 214 62🤣 29👏 26🔥 2🤔 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
በአውስትራሊያ በተፈጸመ የሽብር ጥቃት ዘጠኝ ሰዎች ተገደሉ። በአውስትራሊያ ሲድኒ በሚገኝ የባህር ዳርቻ በተፈጸመ የሽብር ጥቃት ዘጠኝ ሰዎች መገደላቸውን የሀገሪቱ ፖሊስ አስታውቋል። ቦንዲ በመባል በሚታወቀውና በርካቶችን በሚያስተናግደው የባህር ዳርቻ የተፈጸመው ጥቃት በትንሹ 11 ሰዎችን ለጉዳት መዳረጉም ተነግሯል። ሁለት ታጣቂዎች ፈጽመውታል የተባለውን ይህን ጥቃት በርካታ ሀገራትና ዓለም አቀፍ ተቋማት ያወገዙት ሲሆን፤ እስራኤል ይህ ጥቃት በአይሁዶች ላይ የተፈጸመ ነው ብላለች። አውስትራሊያ ግን ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በዚህ ጉዳይ ይፋ ያደረገችው መረጃ የለም። ከጥቃት አድራሾቹ መካከል አንዱ ታጣቂ ወዲያው መገደሉ ሲነገር፣ ሁለተኛው ታጣቂም በከፋ ሁኔታ ውስጥ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH
Показать все...
19😢 14👍 9💯 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ጥገና ቦታ የእሳት አደጋ ተከስቶ ወዲያውኑ ጠፋ አዲስ አበባ — የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባወጣው መረጃ መሠረት፣ ዛሬ ታህሳስ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተርሚናል ውስጥ አነስተኛ የእሳት አደጋ ተከስቶ እንደነበር ተገለጸ። * የእሳት አደጋው የተከሰተው ተርሚናል ሕንፃ ቁጥር 2 ውስጥ ባለው የጥገና ሥራ ቦታ ነው። * መንስኤ፡ ችግሩ የተፈጠረው በብረት ብየዳ ሥራ ወቅት ከተከሰተ ፍንጣቂ ጋር በተያያዘ በአንዲት ትንሽ ክፍል ውስጥ ነበር። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባሰፈረው መግለጫ፣ እሳቱ ወዲያውኑ ምላሽ ተሰጥቶት የጠፋ ሲሆን፣ ምንም አይነት ጉዳት ከማድረሱ በፊት ቁጥጥር ስር መዋል ችሏል። ማረጋገጫ፡ በክስተቱ ምክንያት በመንገደኞች መውጫና መግቢያ እንቅስቃሴ ላይ ምንም አይነት መስተጓጎል አለመፈጠሩን አየር መንገዱ አረጋግጧል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የስታር አሊያንስ አባል፣ ሥራውን በተለመደው ሁኔታ እያካሄደ መሆኑን አስታውቋል።Via Ethio Fm @seledadotio @seledadotio
Показать все...
31🔥 1
በደቡብ ሱዳን ስድስት የተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪዎች ተገደሉ። የተገደሉት ሰላም አስከባሪዎች  ሁሉም ባንግላዲሽያውያን ናቸው። ​የሰላም አስከባሪዎቹ ቅዳሜ ዕለት በኮርዶፋን ክልል ውስጥ በምትገኘው ካዱግሊ ከተማ በሚገኘው ጣቢያቸው ላይ በደረሰ ሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ጥቃት ተገድለዋል። ሰላም አስከባሪዎቹ በአብዬ ጊዜያዊ የሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ አባል ነበሩ። ​ከተገደሉት በተጨማሪ ስምንት ሌሎች የሰላም አስከባሪዎች ቆስለዋል። ​የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በX ባስተላለፉት መልዕክት “በተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪዎች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶች በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት የጦር ወንጀል ክስ ሊያስከትሉ ይችላሉ” ብለዋል። ​የሱዳን ጦር ኃይሎች ድርጊቱን በፓራሚልተሪው RSF ኃይሎች ላይ የቀሰሩ  ሲሆን፣ እነሱ ግን እስካሁን በጉዳዩ ላይ አስተያየት አልሰጡም። ​በተፋላሚ ወገኖች መካከል ያለው ግጭት በቅርቡ ትኩረት ያደረገው በኮርዶፋን ክልል ላይ ነው። የ RSF ኃይሎች በጥቅምት ወር በዳርፉር ክልል የሱዳን ጦር የመጨረሻ ምሽግ የነበረችውን ኤል-ፋሸርን ከተቆጣጠሩ በኋላ ግጭቱ ተባብሷል። ​ኤል-ፋሸር በ RSF ኃይሎች ከተያዘች በኋላ ከፍተኛ ውድመት የታየባት ሲሆን፣ ህዳር መጨረሻ  ላይ በክልሉ በሶስት ሳምንታት ውስጥ በተደረጉ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ቢያንስ 60,000 ሰዎች ተገድለዋል ተብሎ ይገመታል። ​የፓራሚልተሪው RSF ኃይሎች ከ2023 ጀምሮ ከሱዳን ጦር ኃይሎች ጋር በጦርነት ላይ ናቸው። @Addis_News @Addis_News
Показать все...
15😢 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
እንግሊዝኛ ቋንቋን ቤትዎ ቁጭ ብለው ይማሩ Mark Language Academy የእንግሊዝኛ ቋንቋ የመናገር ክህሎትዎን ወይም ችሎታዎን የትም ሳይሄዱ ቤትዎ ቁጭ ብለው Face to Face በ Zoom, በቴሌግራም Video Call ወይም Google meet ላይ መማር ይችላሉ እንዲሁም   አስገራሚ ለውጥ ያመጣሉ ✅ Speaking  ( ንግግር) ✅ Listening ( ማዳመጥ) ✅ Grammar ( ሰዋሰው ) ✅ How to read and Write ( መፃፍ ና ማንበብ ) ሁሉንም በ5 ወር ውስጥ ብቻ ይቻሉና ራስዎን ይለውጡ ከ ሰርተፍኬት ጋር ...... ለመመዝገብ ያናግሩን 👇 @MarkEngAcademy ☎️ 0908880599
Показать все...
7👍 2