68 961
Подписчики
Нет данных24 часа
-137 дней
-96730 день
Архив постов
ምልከታ‼️
#እየሸለምን ያለነው ሀገር ገንቢዎችን ወይስ ጊዜ❗❗ ገዳዮችን? 👉??«#TikTok_Creative_Award»
ከሰሞኑ የተከናወነው የ«TikTok Creative Award» ደማቅ አልባሳት ቅንጦት ና አፍራሽ ተግባራት የታዩበት ሊያሳየን ያልቻለው አንድ አስፈሪ እውነት የሀገራችንን የወደፊት አቅጣጫ የሚወስን ነው።
ጥያቄው፡- እየሸለምን ያለነው ሀገር ገንቢዎችን ወይስ ጊዜ ገዳዮችን? የሚለው ነው።ከበለፀጉት ሀገራት ተሞክሮ አንፃር ሲታይ፣ የዘንድሮው ሽልማት ለወጣቱ ያስተላለፈው መልእክት እጅግ አደገኛ ነው።
Has to be banned!!
ለምን?
1. የቻይናን ጥበብ ወይስ የቻይናን ቆሻሻ? (The Double Standard) የቲክቶክ ባለቤት የሆነችው ቻይና፣ ዓለምን በቴክኖሎጂ የተቆጣጠረችው በመጨፈር አይደለም።
ቻይና ለገዛ ወጣቶቿ የምትፈቅደው የቲክቶክ ቅጂ (Douyin)፣ ከ14 ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት የሚያሳየው የሳይንስ ሙከራዎችን፣ የሮቦቲክስ ፈጠራዎችን እና የአገር ፍቅር ታሪኮችን ብቻ ነው።
ለምን? ምክንያቱም «ነገን የሚረከበው ትውልድ ጭንቅላት በዕውቀት እንጂ መደንዘዝ የለበትም» ብለው ስለሚያምኑ ወደኛ ሲመጣ ግን ነገሩ ተገላቢጦሽ ነው።
ሽልማታችን የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂ፣ የመፅሀፍ እና የበጎ አድራጎት ስራዎችን ወደ ዳር ገፍቶ «ቀልድን» የጀግንነት ማማ ላይ ሰቀለ። ቻይና ለልጆቿ የዕውቀት ወተት ስትግት፣ እኛ ለልጆቻችን በመዝናኛ የተለወሰ መርዝ እየሰጠን ይሆን? ይህንን ቆም ብለን ልንጠይቅ ልንመረምር ይገባል።
2. «Creative» (ፈጠራ) ወይስ «Viral» (ማነጋገሪያ)? ቃላትን በትክክል እንጠቀም። «ፈጠራ» (Creativity) ማለት የህዝብን ችግር የሚፈታ፣ አዲስ እሴት የሚጨምር እና ትውልድን የሚያሻግር ስራ ነው።
ስልክን አገላብጦ በመቅረጽ በሺዎች የሚቆጠሩ «ላይክ» ማግኘት ታዋቂነት (Popularity) እንጂ ፈጠራ (Creativity) ሊሆን አይችልም።
ባደጉት ሀገራት ሽልማት የሚሰጠው ለይዘት ጥራት እና ለሚያመጣው ለውጥ ነው።
እኛ ጋር ግን መስፈርቱ የቁጥር ጨዋታ ሆነ። ሳይንስን፣ ህክምናን እና ትምህርትን የሚያስተላልፉ ቻናሎች እንደ ሁለተኛ ሲታዩ፣ ቀላል መዝናኛዎች የክብር ዙፋን ላይ ተቀምጠዋል። እውቀት በ «ላይክ» ብዛት አይለካም፤ እውነትም በ «ሼር» ብዛት አይረጋገጥም።
3. ለወጣቱ የተላለፈው አደገኛ መልእክት (The Wrong Role Models) አንድ ወጣት ይህንን ሽልማት ሲመለከት አእምሮው ውስጥ የሚቀረፀው ምንድን ነው?
• "ለካ ክብር ለማግኘት ተምሮ ዲግሪ መያዝ፣ ሌሊት ተቀን ለሀገር የሚጠቅም ምርምር ማድረግ ወይም መፅሀፍ መጻፍ አይጠበቅብኝም።"
• "ለካ አቋራጭ መንገድ አለ! ስልኬ ላይ ብጨፍር፣ በቅጽበት 'የዓመቱ ምርጥ' ተብዬ እሸለማለሁ።"
ይህ አስተሳሰብ የስራ ባህልን (Work ethic) የሚገድል መርዝ ነው። አሜሪካን፣ ጃፓንን እና ጀርመንን የገነቡት ፊታቸው በላብ የረጠበ ኢንጂነሮች ሐኪሞች ሙህራኖች ና ገበሬዎች እንጂ፣ ካሜራ ፊት የሚሽሞነሞኑ አይደሉም።
ወጣቱን ትምህርት እና የሥራ ጎዳና አውጥተን፣ ወደ አቋራጭ መንገድ እየገፋነው ነዉ አገርንም ጭምር!
4. የባህል ወረራ በሽልማት ስም
ሽልማቱ ላይ የታየው የአለባበስ እና የቅንጦት ትርኢት፣ የኢትዮጵያን ወጣት ማንነት የሚወክል ነበር? ወይስ የሆሊውድን "Red Carpet" ለመኮረጅ ?
Via:- Dr BEREKET EMMANUEL
MD, Author Founder influential youth Ethiopia CEO
==========≠============
@enlighten_ethiopia
Repost from TgId: 1173613158
ሃይማኖቶችን እከሳለሁ ፥ የሃይማኖት አባቶችን እወቀሳለሁ።
የኢትዮጵያ ህዝብ ከአንድ መከራ ወደ ሌላ መከራ እንዲሸጋገር የተፈረደበት ይመስላል።
በየእለቱ የማያቋርጥ ሰቆቃን ይጋፈጣል። አንድ አንቅፋት ደጋግሞ ይመታዋል።
ባለፉት ጥቂት አመታት በአራቱም አቅጣጫ እሳት እየዘነበ ነው። በምዕራብ ኦሮሚያ እየተደረገ ያለው ጦርነት ንፁሃንን እየቀጠፈ ቢሆንም ማንም ትኩረት አልሰጠውም። የአማራ ክልሉ ጦርነት እስካሁን መፍትሔ አላገኘም። ትግራይ ከጦርነት ሳታገግም ሌላ ጦርነት እየተደገሰ ነው።
በቤንሻንጉል ፥ በጋምቤላ ፥ በሶማሌ ፥ በአፋር... ስላለው ችግር ፍፁም እየተነጋገርን አይደለም።
የሃይማኖት አባቶችን መውቀስ እፈልጋለሁ። ሃይማኖትችን እከሳለሁ።
ሃይማኖት ተቋማትና መሪዎቹን "በሀገር መከራ እጃችሁ አለበት" ብዬ እከሳለሁ። ይህ ማጋነን አይደለም።
በጦርነት ቀጠና አስገድዶ መደፈር መደበኛ ነገር መስሏል። አስገድዶ መድፈር እንደ ጦር መሳሪያ እያገለገለ ነው። የሴቶች ገላ ጦር ሜዳ ሆኗል። ደናግላን በግዳጅ ተነውረዋል። ሚስቶች ከባሎቻቸው ውጭ ወደ ሴትነታቸው ወንድ ገብቷል።
ባል ሚስቱን ከፆታዊ ጥቃት ማዳን አልቻለም። አባት ልጁን ከመደፈር አላዳነም። ወንድም እህቱ እንዳትደፈር ከለላ መስጠት አልቻለም። ይህ ለወንድ ታላቅ ውድቀት ነው።
በዚህ ሁሉ መሃል የሃይማኖት አባቶችን መውቀስ እፈልጋለሁ። የሃይማኖት ተቋማትን እከሳለሁ።
መሐል አገሩ ችግር እየተፈራረቀበት ነው። ፍርድ ይጓደላል ፥ ድሃ ይበደላል። ሙስና ሕጋዊ የሆነ መስሏል። ሰው ሰርቶ መኖር አልቻለም። ቀድሞ ደህና ኑሮ ይኖር የነበረ ዛሬ ወደ ድህነት አረንቋ ተወርውሯል። ኑሮ ተወዷል ተብሎ ብቻ ብሎ መግለፅ ነገሩን ማሳነስ ነው።
የሃይማኖት ተቋማት ማህበራዊ ሃላፊነት የለባቸውም? የሃይማኖት ሰዎች ስለዜጎች አያገባቸውም?
ስለፍትህ ግድ የሚሰጠው ማን ነው?
የእምነት ተቋማት ለነገ እዳ እያከማቹ ነው። ከማንም ቀድመው ኢ-ፍትሃዊነትን ማውገዝ ግዴታቸው ነበር።
ድሃ ሲበደል ፥ ፍርድ ሲጓደል "ይህ ነገር አግባብ አይደለም" የማለት ግዴታ ነበረባቸው። ዜጎች በማንነታቸው ሲጠቁ "ሕግ ይከበር ፥ ይህ ነውር ይቁም" ማለት ግዴታቸው ነበር።
ጉልበተኛ ደካማውን ሲጎዳ ዝም ማለት አልነበረባቸውም። ለድምጽ አልባው ድምጽ መሆን ነበረባቸው።
ዝም ብለዋል። መናገር የነበረባቸው ዝም ብለዋል።
ቀሳውስት ዝም ብለዋል።
ፓስተሮች ዝም ብለዋል።
ኡስታዞች ዝም ብለዋል።
የሃይማኖት አባቶች ዝምታን መርጠዋል። አገር እየተናጋ እነርሱ በዝምታ አድፍጠዋል።
ምናልባት ይፈሩ ይሆናል። "ብንናገር እናልቃለን" የሚል ስጋት ይኖርባቸው ይሆናል። ነገር ግን ፈርተው ዝም ያሉቱ ግብዞች መሆናቸውን አሳይተውናል።
ለእውነት ሲሉ ዋጋ መክፈል ለእምነት አባት ክብሩ ነው። ከእውነትጋ ተባብሮ ፥ ለፍትህ ድምፅ ሆኖ መከራን መቀበል ለሃይማኖት አባት ጌጡ ነው።
የእምነት ተቋማት ፥ የሃይማኖት አባቶች ለደካማው ድምጽ መሆንን ካልወደዱ ስለ ፍትህ የመናገር ሞራል ይኖራቸዋል? ለእውነት ሲሉ ዋጋ ሳይከፍሉ ስለ እውነተኝነት መስበክ ይቻላቸዋል?
አምላክ ፍትሃዊ ነው። ፍትሃዊ አምላክን ካመለካችሁ ለደካማው ድምጽ ሁኑ!
ይህ እስኪሆን ድረስ የሃይማኖት ተቋማትን እወቅሳለሁ ፥ የሃይማኖት አባቶችን እከሳለሁ።
"በዝምታችሁ ኢ-ፍትሃዊነትን ተባብራችኋል ፥ ባለመናገር በደልን አግዛችኋል" ብዬ እከሳቸዋለሁ!
Via ተስፋኣብ ተሾመ
@Tfanos
❤ 67👍 17🤔 6😢 6🔥 4
..የቀጠለ
በዚህ ጊዜ ሽማግሌው በዝግታ ተናገረ፡- ‹‹ለበርካታ ዓመታት በባሃማስ እኖር ነበር።››
ዶ/ር ማይልስ ይህን ጊዜ ፈገግ ብሎ ጥያቄውን አዥጎደጎደ፡-
‹‹እውነትዎን ነው? መቼ ነበር? የትኛው ከተማ?››
‹‹በዋናው ከተማ ናሳዉ ነበር›› አለ፡
‹‹በዚያ ሥራዎ ምን ነበር?›› ሌላ ጥያቄ ዶ/ር ማይልስ ወረወረ።
‹‹አስተማሪ ነበርኩ!›› አለ፡
‹‹ምን ተብሎ የሚጠራው ትምህርት ቤት?›› የዶ/ር ማይልስ የማወቅ ፍላጎት በረታ። ሽማግሌው የትምህርት ቤቱን ስም ጠራለት።
‹‹እንዴ! ጌታዬ እኔም እኮ እዚያ ነበር የተማርኩት›› አለ ዶ/ር ማይልስ።
‹‹አዎ! ምናልባት አንተ አታስታውስኝ እንደሆነ እንጂ እዚያ አስተማሪ ነበርኩ›› አለው።
‹‹ይቅርታ ያድርጉልኝ! በፍፁም ላስታውስዎት አልቻልኩም›› አለ ዶ/ር ማይልስ ወንበሩ ላይ እየተቁነጠነጠ።
‹‹እኔ ሚስተር ሮቢንሰን ነኝ›› አለው፡፡
ዶ/ር ማይልስ ደስታና ድንጋጤ በተቀላቀለ መንፈስ ጮኸ፡-
‹‹ሚስተር ሮቢንሰን!!››
ከዓመታት በፊት የዝንጀሮ ዘር፣ ባርያ፣ ግማሽ ሰው፣ ዘገምተኛና ደደብ በማለት ሲጠራው የኖረው ይህ አስተማሪው እንደነበር በድንገት ትዝ አለው፡፡
ዶ/ር ማይልስ በዚህ ጊዜ ከወንበሩ ተስፈንጥሮ በመነሳት ወደሽማግሌው ተንደረደረ፣ አጠገቡ ደርሶም በሁለት እጆቹ አቅፎ ናፍቆቱን ገለፀለት፡፡
ሽማግሌው ቲቸር ሮቢንሰን ግን በዶ/ር ማይልስ ትከሻ ላይ ጭንቅላቱን አስደግፎ ማልቀስ ጀመረ። በሥፍራው የነበረ ሁሉ እነዚህ ጥቁርና ነጭ ሰዎች በናፍቆት ጉንጭ ለጉንጭ እየተሳሳሙ ተቃቅፈው ሲላቀሱ እንደድራማ እነሱን እየተመለከተ ፈዘዘ።
ሽማግሌው ሮቢንሰን፡- ‹‹አዝናለሁ! አዝናለሁ! አዝናለሁ!›› እያለ ደጋግሞ ይቅርታ መጠየቁን ይዞታል።
ዶክተር ማይልስ አሁን መሳቅ ጀመረ፡- ‹‹እውነት እንደው ሚስተር ሮቢንሰን በዝንጀሮ፣ የፍጡር ሂደቱን ባልጨረሰ ግማሽ ሰው፣ ደደብ፣ ጠቋራ ባርያ የተፃፈ መጽሐፍ አነበብኩ እያሉኝ ነው? ዝንጀሮ ሕይወቴን ለወጠው እያሉኝ እኮ ነው!?›› ከዚያ በኋላ ሁለቱም ተያይዘው ለረዥም ሰዓት መሳቅ ጀመሩ፡፡
‹‹ውድ አስተማሪዬ !! ማንኛውንም የሰው ልጅ በድጋሚ ዝቅ አድርገው እንዳይመለከቱ! ፈጣሪ በውስጡ ያስቀመጠው ምን እንደሆነ አያውቁትምና!›› ሲል ዶ/ር ማይልስ የሰንብት ምክር ጣል አደረገ፡፡ ዶ/ር ማይልስ ዝንጀሮ ተብሎ በተሰደበበት በዚያ ትምህርት ቤት ውስጥ ዛሬ አንዱ ማስተማሪያ የእሱ መጽሐፍ ሆኗል፡፡
ወድ አንባቢዬ! ዛሬ በሕይወት ውስጥ የምትገኝበትን ሥፍራ ምን ወይም የት እንደሆነ ማወቅ አልችልም፣ ነገር ግን አንድ እውነት ቢኖር ሰዎች የፈለጉትን ዓይነት በርካታ ስም እየለጠፉብህ ሊጠሩህ ይችላሉ፣ ነገር ግን አንተ ለራስህ ከሰጠኸው አንድ ስም ጋር ፈፅሞ ሊወዳደር እንደማይችል እመን!!
የስብዕና ልህቀት
@enlighten_ethiopia
"በፍፁም በራስህ ላይ ተስፋ አትቁረጥ"
ማይልስ ሞንሮ የአስራ አራት ዓመት ልጅ እያለ በተወለደባት ባሃማስ ደሴት አንድ ትምህርት ቤት ውስጥ የስድስተኛ ክፍል ተማሪ ሆኗል። ታዲያ ነጩ ስኮትላንዳዊ አስተማሪ ሚስተር ሮቢንስን በዚያ ትምህርት ቤት የሚማሩ ጥቁሮችን ዘውትር ያላግጥባቸዋል፣ ያንቋሽሻቸዋል፡፡ ‹‹ምንም የማይገባቸው ደደቦች ፣የድንጋይ ራሶች፣ እንስሶች...›› የጥቁሮችን ማንነት የሚገልጥበት የየዕለትት ቋንቋው አድርጎታል። አንድ ቀን የስድቡ ተራ ለማይልስ ደረስ፡-
" አንተ ከእንስሳ የተዳቀልክ ግማሽ ዝንጀሮ፣ የአእምሮ ዝግመት ተጠቂ፣ ጠቋራ ባሪያ፣ በመጥረቢያ ጭንቅላትህን ከፍቼ መጽሐፍትን ብጨምርብህ እንኳን ትምህርቱ አይገባህም›
ይኽን የመምህራኑን ውርጅብኝ ያስተናገደው ማይልስ እግረመንገድ የእስከዛሬ የትምህርት ውጤቱን መለስ ብሎ ቢያስበው እውነትም እንደአስተማሪው ነቀፋና ማላገጥ ‹‹F›› ብቻ ሆነበት፡፡ ‹‹በቃ ሚስተር ሮቢንስን እውነቱን ነው፤ ትምህርት ለእኔ አይገባም›› ሲል ከውሳኔ ደርሶ ወደቤቱ አመራ፡፡ ከቤቱ ሲደርስ የሆነበትን ሁሉ ለእናቱ እያለቀሰ ተርኮ ሲያበቃ ከእንግዲህ ትምህርት ቤት የመመለስ ፍላጎት እንደሌለው ጨምሮ ነገራት፡፡
እናቱ ግን ጠቢብ ሆነች፡፡ እንደሚስተር ሮቢንሰን ስለልጇ ከአንደበቷ ከፉ ቃል አልወጣም ወይም ማይልስ ለራሱ በሰጠው ግምትም አልተቆጣችውም። በዝምታ ወደመኝታ ቤቷ አመራች፤ አፍታም ሳትቆይ ደግሞ በእጇ አንድ መጽሐፍ ጨብጣ ተመለሰች፡፡
‹‹ማይልስ! እንካ ይሄንን ተቀምጠህ በዕኖና አንብበው›› ፈገግ ብላ ከእጆቹ አኖረችለትና ‹‹መጽሐፍ ቅዱስ ይባላል›› ስትል ደግሞ አስተዋወቀችው፡፡
ማይልስ ከእጆቹ ላይ የተቀመጠውን መጽሐፍ ሽፋኑን አገላብጦ በሚገባ ካጠናው በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ውስጡን : ገለጠው፡፡ ዐይኑ ያረፈበት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ እንዲህ የሚል ሆኖ አገኘው፡- "እንግዲህ በእኛ እንደሚሠራው ኃይል መጠን ከምንለምነው ወይም ከምናስበው መጠን ይልቅ እጅግ አብልጦ ሊያደርግ ለሚቻለው...›› (ኤፌ 3፡20)፡፡ በነጋታው ይህን አጋጣሚ በሚመስል ሁኔታ ለመጀመሪያ ጊዜ መጽሀፍ ቅዱስ ሲገልጥ ያነበበውን ጥቅስ እያሰላሰለ ወደ ትምህርት ቤቱ ማልዶ ገሰገሰ፡፡ ከሦስት ወር በኋላ የፈተና ውጤት ሲነገር በሁሉም ‹‹B›› ማግኘቱ ተነገረው፡፡ ቀጣዩ ሴሜስተር ደርሶ የፈተና ውጤት ተለጠፈ፡፡ ማይልስ በሁሉም ፈተናዎች ‹‹A›› አግኝቷል። ከዚያ በኋላ ባሉት ዓመታት በነበረው የትምህርት ቤት ቆይታው ከክፍሉ ብቻ ሳይሆን ከትምህርት ቤቱ ተማሪዎች ሁሉ ልቆ አንደኛ በመውጣት ጨረሰ፡፡
የተማሪዎች ምረቃ ቀን ማይልስ ወደ መድረክ ተጠርቶ የክፍተኛ ማዕረግ ተመራቂነትን ክብር ተቀዳጀ፤ ሽልማትም ተሰጠው። ፈረንጅ ተማሪዎች ሳይቀሩ ከመድረኩ ሥር ተቀምጠው ለማይልስ ያጨበጭባሉ። ማይልስ ሽልማቱን ተቀብሎ በቀጥታ ያመራው ወደ ሚስተር ሮቢንሰን ነበር፡፡ ‹‹እነሆ ውድ መምህሬ! እኔ ግማሽ ዝንጀሮ የሆንኩት ዛሬ ይሄን ሽልማት ለመታሰቢያ ያህል ለአንተ አበረከትሁልህ..›› ፈገግ ብሎ ከእጆቹ አኖረለት
ይህ ከተፈፀመ ከጥቂት ዓመታት በኋላ ማይልስ ወደ ኮሌጅ አምርቶ
በአራት ዓመታት ውስጥ ሦስት ባችለር ዲግሪዎችን ተቀበለ፡፡ ከዚያ ቀጠለና በዓመት ከስድስት ወሩ የማስተርስ ዲግሪውን በክብር አገኘ፡፡ ከዚያ በኋላ በመጡት በርካታ ዓመታት ያ የዝንጀሮ ዘር፣ የአእምሮ ዝግመት ተጠቂ እንዲሁም ደደብ የተባለው ማይልስ አምስት ዶክትሬት ዲግሪዎችን ከአምስት የተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ለመቀበል በቃ። እንዲሁ ለቁጥር የሚታክቱ ድንቅ መጻሕፍትንም ደርሶ ለዓለም አበረከተ፡፡
አንድ ቀን በለንደን በመሪነት ጥበብ ርዕስ ዙሪያ በተዘጋጀ ሴሚናር ላይ ማይልስ ተጋባዥ እንግዳ ሆኖ ተገኝቷል። ንግግር አድርጎ ጨርሶ ከሆቴሉ የእንግዳ መቀበያ በተዘጋጀለት ሥፍራ ላይ መጽሐፉን ገዝተው ፊርማውን ከፊት ለፊቱ ተሰልፈው ለሚጠብቁት አንባቢዎቹ ለመፈረም ተቀመጠ፡፡ የሰልፉ ርዝመት መቼም አይነገርም። እየፈረመ፣ እየፈረመ ቆይቶ አንድ በምርኩዝ ድጋፍ የሚጓዝ ሽማግሌ ፈረንጅ ተራው ደረሰና ከፊቱ ቆመ። በመነበብ ብዛት እጅግ ያረጁ፣ ስርዝ ድልዝ በገጾቻቸው የሞላባቸው ሁለት መፅህፍትን ይዟል። ሰውዬው አረማመዱ መጃጀቱን ያሳብቅበታል፡፡
ዶ/ር ማይልስ የመፃህፍቶቹን ማርጀትና በስርዝ ድልዝ መሞላት ተመልክቶ ወደ ፈረንጁ በፈገግታ ቀና አለ፡- ‹‹ጌታዬ! መጽሐፎቼን እንዲህ ሆነው ከማየት በላይ የሚያስደስተኝ ነገር የለም፡፡ የገዛቸው ሰውዬ በሚገባ አንብቧቸዋል ማለት እኮ ነው! በጣም አድርጌ አመሰግንዎታለሁ!››
ሽማግሌው ሰውዬም፡- ‹‹እነዚህ መጻሕፍት ሕይወቴን እስከወዲያኛው ለውጠውታል›› አሉት።
የማይልስ ደስታ አይነገርም፡- "በጣም አመሰግንዎታለሁ! አሁን የተናገሩት ለእኔ ምን ማለት እንደሆነና ሊፈጥርብኝ የቻለውን ስሜት - የሚረዳው ደራሲ የሆነ ብቻ ነው›› ሲል በአክብሮት ምስጋናውን አስቀድሞ ፊርማውን አኑሮ መፃህፍቱን መለሰ፡፡ ሽማግሌው ሰውዬ ግን መፃህፍቱን ተቀብሎ አልሄደም፤ እዚያው እንደቆመ ቀረ።
ዶ/ር ማይልስ ከፊቱ ተገትሮ በቀረው ሰው ግራ ተጋብቶ ‹‹ጌታዬ! ከኋላህ ብዙ ሰው ተሰልፎ ፊርማዬን እየጠበቀ ነው፡፡ እባክህ ሥፍራውን ልትለቅላቸው ትችላለህ።" አለው፡፡
ሽማግሌው የሰማው አይመስልም፡፡ አትኩሮቱን ሁሉ ዶ/ር ማይልስ ላይ ጥሎ በአንክሮ ይመለከተዋል።
‹‹ጌታዬ! ወደዚህ ሥፍራ አክብረኽኝ ስለመጣህ፣ እንዲሁም መፃህፍቴን ስለምታነብ አክብሮቴ የላቀ ነው፡፡ ነገር ግን እባክህ ብዙ ሰው ከኋላህ ቆሟል...›› ሲል በድጋሚ ጠየቀው። ሽማግሌው ግን አሁንም በዝምታ ተውጦ እንዳፈጠጠበት ቀረ።
በሁኔታው የተጨነቀው ዶ/ር ማይልስ፡- ‹‹ጌታዬ! ችግር ይኖር ይሆን እንዴ? ወይም ልትነግረኝ የፈለግኸው ነገር አለ?›› አለው፡፡
ይቀጥላል ...
❤ 48👍 3👏 2🔥 1
Repost from TgId: 1173613158
የቲክቶክ አዋርድ ፥ እንደ ፖለቲካ ማሳያ
* * *
በቲክቶክ አዋርድ በኩል ብናጮልቅ የፖለቲካ ንቃተ ህሊናችንን እንመለከታለን።
ለቲክቶክ አዋርድ ፥ድምፅ የሚሰጡ ሰዎች ድምፅ የሚሰጡት አቅምን ታሳቢ አድርገው አይደለም። ዋነኛ መስፈርታቸው ቡድንተኝነት ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ህዝበኝነት ነው።
አንዳንዶች የሃይማኖት ካርድ መዘዋል። የእምነታቸው ተከታይ እንዲያሸንፍ ጠብ እርግፍ ይላሉ። ነገርዬውን ሃይማኖታዊ ተጋድሎ አድርገውታል። ሌሎች የብሔር ካርድን መዘዋል። ለፌደሬሽን ምክር ቤት ተወካይ የሚያቀርቡ ይመስል ተፍ ተፍ እያሉ ነው። እግር ኳስም ጭምር ከውግንና ፖለቲካው አላመለጠም።
እግር ኳስ ከውግንና ፖለቲካ የሚለይ መዝናኛ ነው። ነገር ግን የዘንድሮ የቲክቶክ አዋርድ ይህን መርህ ጥሷል።
ጥሩ የስፖርት መረጃ አቅራቢ ማነው? ቲክቶክ ላይ ጥሩ የስፖርት መረጃ የሚያቀርቡ ብዙ ሰዎች አሉ። ማሸነፍ ይገባቸዋል። ነገር ግን መራጮች መስፈርታቸው ቡድንተኝነት ነው!
"የአርሰናል ደጋፊዎች እገሌን ምረጡ፥ የዩናይትድ ደጋፊዎች ለእንቶኔ ድምፅ ስጡ" ይባላል። መስፈርቱ የቡድን ውግንና ሆኗል።
ሌላው የመራጮች ድምፅ ላይ ተፅዕኖ ያሳደረው ፖፑሊስትነት ነው።
ጥሩ ይዘት ፈጠራን ከበጎ አድራጎትጋ ይደበላልቁታል። ጥሩ ይዘት የሌለው ግን የደግነት ምልክት ያሳየ ሰው "ባለ ጥሩ ፈጠራ" ተብሎ ድምፅ ይሰጠዋል። እንዴት የሚል ጥያቄ ሲነሳ "ደግ ሰው ነው" ይባላል። ስለ ደግነት መች ተጠየቀ?
የቲክቶክ አዋርድ የፖለቲካ ንቃተ ህሊናችንን ይናገራል።
ለማህበራዊ ሚዲያ ሽልማት የቡድን ውግንናን ቅድሚያ የሰጠ ሰው የፖለቲካ ምርጫን እንዴት ይመለከተዋል?
ለቲክቶክ አዋርድ ከብቃት ይልቅ ሀይማኖት ፥ ብሔር እና የእግርኳስ ቡድን ድጋፍ ዋነኛ መመዘኛ ያደረገ ሰው ፖለቲካን በብቃት ይመዝናል? በፍፁም!
ለቲክቶክ አዋርድ ከብቃት ይልቅ በጎ አድራጎትን መስፈርት ያደረገ ሰው ለፖለቲካ ምርጫ መስፈርቱ ምን ይሆናል?
እንዲህ አይነት መራጭ ፥ ብቁ ያልሆነ ነገር ግን የደግነትን ጭንብል ያጠለቀ ጮ ሌ አያታልለውም?
ዴሞክራሲ ለብዙሃን ድምፅ ዋጋ ይሰጣል። እንደ አቅሚቲ "ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ይደረግ" የሚል ጥያቄ አለን። ደግሞም ከፊታችን ምርጫ ይደረጋል።
ምርጫው ላይ መንግስት ፍትሃዊ ምርጫ ላያደርግ ይችላል የሚል ጉልህ ስጋት አለ። ስጋቱን እንርሳውና ፍትሃዊ ምርጫ ቢደረግስ?
በእርግጥ ፍትሃዊ ምርጫ ቢደረግ ጠቃሚ አካል እንመርጣለን?
የምርጫችን መስፈርት ምንድነው?
ከብቃት ይልቅ ግለሰባዊ ቸርነት እና ቡድናዊ ውግንናን ቅድሚያ የሚሰጥ ማህበረሰብ ፥ በራሱ ላይ አ ው ሬ ን ይሾማል!
Via ተስፋኣብ ተሾመ
@Tfanos
👍 57❤ 43🤣 5👏 4😢 2🔥 1
☞ መንፈሰ ጠንካራ ሰዎች የማያደርጓቸው አስሩ ነገሮች፡
መንፈሰ ጠንካራ ሰዎች ሃሳባቸውንና ባህሪያቸውን በመግራትና ስሜታቸውን በመቆጣጠር ይታወቃሉ ፡፡ በአዕምሯዊ #ብስለትና በአስተሳሰብ ከፍ ያለ ደረጃ ላይ የደረሱ ሰዎች የሚከተሉትን ነገሮች አያደርጉም ፡፡
➊. ፍርሃት የለባቸውም
መንፈሰ ጠንካራ ሰዎች #ምክንያታዊ አስተሳሰብን ስለሚያጎለብቱ ሰዎች ብዙ ጊዜ በማህበራዊና በኢኮኖሚያዊ ህይወታቸው ወደፊት ሊገጥማቸው ስለሚችሉ ችግሮች አስቀድመው ስጋት ውስጥ ለሚጥል ጭንቀት አይዳረጉም ፡፡
➋. በሌሎች ስዎች ስኬታማነት አይቀኑም
አዕምሯቸው ሚዛናዊነትን ያጉለበተ ሰዎች ስኬትን ከተቀዳጁ ሌሎች ሰዎች ትምህርትን ለመውሰድ ሙሉ በሙሉ ዝግጁ እንደሆኑ ይነገራል ፡፡ የስነ ልቦና ባለሙያዎች በሌሎች ሰዎች ድክመትና ስኬትማነት ላይ ማተኮር የራስን እቅድ ያሳጣል ይላሉ ፡፡
➌. ባለፈ ነገር አይፀፀቱም
ስላለፈው ጉዳይ መጨነቅና በፀፀት ጊዜን ማሳለፍ ለወደፊቱም እቅድን እንዳይነድፉ መሰናክል ይሆናል ፤ መንፈሰ ጠንካራ ሰዎች ካለፈው ችግራቸው ወይም ውድቀታቸው ትምህርት በመውሰድ አሁን ያለውን የተሻለ በማድረግ ለነገ ስኬታማነታቸው በጥረት ይሰራሉ ፡፡
➍. ራሳቸውን አሳልፈው አይሰጡም ፤ አይሸነፉም
ብዙ ጊዜ መንፈሰ ጠንካራ ሰዎች አካላቸው እንኳ ቢደክም በአስተሳሰብና በአመለካከታቸው ብርቱ አቋም ይዘው ለስኬት ይበቃሉ ፡፡ ራሳቸውንም ለጠላቶቻቸው አንበርክከው አይሰጡም፡፡
➎. ለውጥን አይፈሩም
እነዚህ ሰዎች ነገሮችን አመዛዝነው የሚተነብዩ በመሆናቸው በሚያደርጉት ማንኛውም ነገር ለሚመጣው ውጤት ዝግጁ ናቸው ፡፡
➏. ከአቅማቸው በላይ በሆነ ጉዳይ ጊዜያቸውን አያባክኑም
በአዕምሯዊ ብስለታቸው ከፍ ያሉ ሰዎች ሁሉም ነገር እነሱ ባቀዱት ልክ እንደማይሆንና ከአቅማቸው በላይ የሆነ ነገር እንደሚኖር ስለሚያስቡ አይጨነቁም ፡፡ ከአቅማቸው በላይ ሆነው ለጭንቀት የሚዳርጉ ነገሮችን በአግባቡ በማስተናገድም ካልተገባ ውጥረት ራሳቸውን ያድናሉ ፡፡ በዚህም ሰኬታማነታቸውን ያጎለብታሉ ፡፡
➐. ተመሳሳይ ስህተት አይሰሩም
ብዙ ጊዜ ስህተት በድጋሚ ሊከሰት የሚችለው ያለፈውን ካለማገናዘብና እንዳይደገም ካለመዘጋጀት እንደሆነ የስነ ልቦና ምሁራን ናገራሉ ፡፡ ጥሩ የአዕምሮ ብስለት ያላቸው ሰዎች ደግሞ ለሚሰሩት ስህተት ኃላፊነትን በመውሰድ በቀጣይ እንዳይደገም መፍትሔ አስቀምጠው ይሰራሉ ፡፡
➑. በመጀመሪያው ውድቀታቸው አይሸነፉም
አዕምሯዊ ጥንካሬ ያላቸው ሰዎች በመጀመሪያው ውድቀታቸው መሸነፍን አያውጁም ፤ ከውድቀታቸው ትምህርትን በመውሰድ የተሻለ ውጤትን ለማምጣትም በትጋት ይሰራሉ ፡፡
➒. ቅፅበታዊ ውጤትን አይጠብቁም
አስተሳሰባቸው ከፍ ያሉ ሰዎች ብዙ ጊዜ የሚሰሩት ስራ ወዲያውኑ ውጤት እንደሚያስገኝላቸው በማሰብ አይጓጉም ፡፡ ከዚህ ይልቅ ሁሉ ስራ የራሱ ጊዜ እንዳለውና የስኬቱም ምንጭ የተቀመጠለት ጊዜ ፣ የሚደረግለት ተግባራዊ እንቅስቃሴ መሆኑን በእቅዳቸው አስቀምጠው ጉዞ ወደ ፊት ይላሉ ፡፡ ይህ ደግሞ ምክንያታዊ ወይም እውናዊ የስኬት ምንጭ በአንድ ሌሊት እንደማይመጣ መረዳትን ያሳያል ነው ያሉት ባለሙያዎቹ ፡፡
➓. ዓለም ሁሉንም ነገር እንድታበረክትላቸው አይፈልጉም
ዓለማችን ብዙ ተቃርኖዎች ስኬትና ውድቀት ፣ ሀብትና ድህነት ፣ ሀዘንና ደስታ ወዘተ የተጣመሩባት እንደመሆኗ መንፈሰ ጠንካራ ሰዎች የሚፈልጉትን ሁሉ ከዓለም እንዲያገኙ አይፈልጉም ፡፡ ከዚህ ይልቅ በዓለም ላይ ደስታም ሆነ ሀዘን ፣ ስኬትም ሆነ ውድቀት የሚያጋጥመው በራስ ጥረትና ጥንቃቄ ልክ ነው ብለው ያምናሉ ።
የስብዕና ልህቀት
@Human_Intelligence
👍 61👏 8❤ 2😢 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
ምርጡ ፊልም አይተህ የወደድከው ነው - ኦስካር የወሰደው አይደለም...
ምርጡ ሙዚቃ የልብህን ያዜመው ነው - ግራሚ ያሸነፈው አይደለም...
ምርጡ ምግብ ተርበህ ያገኘኸው ነው - ጣፍጦህ የበላኸው አይደለም...
ምርጡ መጽሐፍ ውስጥህን ያነበበው ነው - አንተ ያነበብከው አይደለም...
ምርጡ ስጦታ ድንገት የመጣው ነው - ውድ ያወጣው አይደለም...
ምርጡ ጓደኛህ ያልነገርከውን የሚሰማው ነው - እስክትነግረው የሚጠብቀው አይደለም...
ምርጡ ጊዜ አሁን ነው - የሚመጣው አይደለም...
ምርጡ ሃብት ፍቅር ነው - ገንዘብህ አይደለም...
ምርጡ መንገድ የማትጋፋበት ነው - አስፓልት አይደለም...
ምርጡ ቤት እንቅልፍ የሚሰጥህ ነው - ውብ ሕንፃ አይደለም...
ምርጡ ስልጣን ራስን መግራት ነው - ሌላውን መግዛት አይደለም...
ምርጡ እውቀት ራስን ማወቅ ነው - ያጠኑትን ማስታወስ አይደለም...
ምርጡ ቃል በወቅቱ የተነገረው ነው - በዘይቤ ያጌጠው አይደለም...
ምርጡ ሰው ራሱን የሆነው ነው - መንጋው የከበበው አይደለም...
ምርጡ ባለውለታህ አቅምህን ያሳየህ ነው - ጥሪት ያኖረልህ አይደለም...
~
እና ደግሞ...
__
ምርጥነት ለሌሎች እንደሚታየው አይደለም... ለራስ እንደሚሰማው እንጂ...
~
@bridgethoughts
👍 89❤ 32🔥 4👏 2
የማስተካከል ድንቅ ጥበብ
በመጀመሪያ ለሕይወታችን እቅድ እንሰራለታለን፡፡ አንደኛ እቅድ ትምህርት፣ ስራ፣ የፍቅር ሕይወት፣ ቤተሰብ እያልን እናድጋለን፡፡ ከዚያም ወደ ሕይወት ግቦቻችን እንደርሳለን። በእርግጥ እንደዚያ እንደማይሰራ እንደምታውቅ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ሕይወታችን ማባሪያ በሌለው ብጥብጥና ግርግር ውስጥ ታልፋለች፡፡ የሕይወታችን አብዛኛውን ጊዜያችንን የምናጠፋውም ባላየናቸው የሕይወት ውጣ ውረዶች የሚመጡብንን ፈተናዎች በመታገል ነው፡፡
በህይወት ውስጥ ወሳኙ ነገር መነሻው ሳይሆን ከመነሻው በኋላ የሚመጡት የማስተካከያ ጥበቦች መሆናቸውን ተምሬያለሁ። ከብዙ ቢሊዮን ዓመታት በኋላ ተፈጥሮም ይህን - የተማረች ትመስላለች። ህዋሳት በተከፈሉ ቁጥር የመቅዳት ሂደት ስህተቶች (copying errors) ቀጣይነት ባለው መልኩ በዘረመላዊ ቁሶች ውስጥ እየተፈጠሩ ይሄዳሉ፡፡ ስለሆነም በእያንዳንዱ ህዋስ ውስጥ እነዚህን ስህተቶች ወደኋላ ተመልሰው የሚያስተካክሉ ሞለኪዮሎች አሉ። የዲ ኤን ኤ ጥገና ባይኖር ኖሮ ልክ እንደተወለድን በሰዓታት ውስጥ በካንሰር አማካይነት መሞታችን አይቀርም ነበር፡፡ የበሽታ መቋቋም ሥርዓታችን የሚሰራውም በተመሳሳይ መልኩ ነው። ችግሮች ቀድመው የማይታዩ በመሆናቸው ምክንያት ቀድሞ የተዘጋጀ ማስተር ፕላን የለም፡፡ ቫይረሶችና ባክቴሪያዎች በየጊዜው እየመጡ ሰውነታችንን ያጠቃሉ። የመከላከል ሥርዓታችንም ሁልጊዜ ይሄንን በማስተካከል ይሰራል።
ስለዚህ ወደፊት ሁለት በጣም የማይጣጣሙ ጥንዶች መካከል የሰመረ ትዳር መመስረቱን ስትሰማ ብዙ አትደነቅ፡፡ ይህ የስሪትን (set up) አጋኖ የማየት አይነተኛ ምሳሌ ነው፡፡ በግልጽ ካወራን የትኛውም ሰው ለትንሽ ሰዓት በግንኙነት ውስጥ ከቆየ ያለማስተካከያና ያለማሻሻያ ግንኙነቱ መቀጠል የማይችል መሆኑን ይረዳል። የትኞቹም ጓደኝነቶች ማደግ አለባቸው፡፡
ብዙውን ጊዜ ከማያቸው የተሳሳቱ አረዳዶች መካከል አንዱ ‹ጥሩ ሕይወት ማለት የተረጋጋ ሁኔታ ውስጥ መኖር ማለት ነው› የሚለው ድምዳሜ ነው፡፡ ይህ ስህተት ነው፡፡ ጥሩ ሕይወት . የሚመጣው ቀጣይነት ባላቸው የዘወትር ማሻሻያዎች ውስጥ በማለፍ ነው፡፡
እና እኛ ለማስተካከልና ለመሻሻል የምናቅማማው ለምንድን ነው? ምክንያቱም እያንዳንዷን የማስተካከያ ስራ የምንረዳት በመስመራችን ላይ እንደተገኘ ድክመት ስለሆነ ነው፡፡ በእርግጠኝነት እቅዳችን እየሰራ አለመሆኑን እንናገራለን፡፡ በዚህም የውርደት ስሜት ይሰማናል፡፡ እውነታው ግን ሌላ ነው፡፡ እቅድ እንደወረደ ሰርቶ አያውቅም፡፡ ድንገት ያለምንም እንከን ሰርቶ የሚያውቅ ከሆነም እንኳን ሁኔታው ፍፁም አጋጣሚ ነው፡፡
ታዋቂው የአሜሪካ ጀኔራልና በኋላም ፕሬዝደንት) ዋይት ኤዘንሃወር እንዳለው “እቅዶች ምንም አይደሉም፧ ማቀድ ግን ሁሉ ነገር ነው፡፡” ነገሩ ወጥ የሆነ ፅኑ እቅድ ስለመያዝ አይደለም፤ በተደጋጋሚ እና ሁልጊዜ የሚኖር የማቀድና የማሻሻል ሂደት እንጂ።
“ወታደሮችህ ልክ የጠላትን ጦር ሲያገኙ” ይላል ኤዘንሃወር “የትኛውም እቅድ ጥቅም አልባ ይሆናል፡፡
ህገ መንግስታት ሁሉም ህጎች የሚያርፉባቸውን መሰረቶች የሚጥሉ የበላይ ሰነዶች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሁሉም ህገ መንግስታት በመሻሻል ሂደት ውስጥ ያልፋሉ። ለምሳሌ በ1787 የፀደቀው የአሜሪካ ህገ መንግስት እስካሁን ባለው ዘመኑ 27 ጊዜ ተሻሽሏል። የስዊዘርላንድ ህገ መንግስትም ከ1848 በኋላ ሁለት ትልልቅ ማሻሻያዎችን (revisions) እና በርካታ ጥቃቅን ማስተካከያዎችን አስተናግዷል፡፡ የጀርመኑ የ1949 ህገ መንግስት በበኩሉ 60 ያህል ማሻሻያዎች አይቷል፡፡
ይህ ውርደት ወይም ድክመት አይደለም፡፡ ትርጉም የሚሰጥ ሂደት እንጂ። የማስተካከል አቅም የየትኛውም
ዴሞክራሲያዊ ማህበረሰብ መሰረት ነው፡፡ ዴሞክራሲ የሚገነባው በማስተካከያ ስርዓቶች ውስጥ ነው፡፡ በወጉ የሚስራው ብቸኛው የመንግስት አይነትም ይሄ ነው፡፡
እንዳለመታደል ሆኖ በሌሎች ሁኔታዎች ላይ ያላን የማስተካከል ፍላጎት ደግሞ ዝቅ ያለ ነው፡፡ የትምህርት ስርዓታችንን
መጥቀስ ይቻላል። የትምህርት ስርዓታችን በእውነታ እውቀት እና በሰርተፍኬት (ስሪት) ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ በዲግሪ እና በስራ ቦታ ውጤታማነት መካከል ያለው ክፍተት ግን ብዙ ነው። ይሄንን እያስተካከልን አይደለም፡፡
በባህሪ እድገታችንም ውስጥ ተመሳሳይ ነገር አለ፡፡ አንድ ብልህና አስተዋይ የምትለው ሰው እንደሚኖርህ እርግጠኛ ነኝ፡፡ የዚህ ሰው አስተዋይ መሆን ዋና ምክንያቱ ምን ይመስልሃል? ስሪቱ? .
(ትክክለኛ ዘር፣ ጥሩ አስተዳደግ፣ ጥራት ያለው ትምህርት) ወይስ የማስተካከል ልምዱ? (በሕይወቱ የሚያያቸውን ክፍተቶችን በየጊዜው እያስተካከለ የመሄድ ችሎታው?)
ሲጠቃለል; ለማስተካከል ያለንን መጥፎ አተያይ ማስወገድ አለብን። ትክክለኛውን - ህግ እንከተላለን ብለው እየታገሉ እድሜያቸውን ከሚያቃጥሉ ሰዎች ይልቅ በጊዜ ራሳቸውን ማስተካከል የጀመሩ ሰዎች የበለጠ ተጠቃሚ ናቸው። ፍፁም የሚባል ልምምድ እና ህግ የለም። የሕይወት ግቦችም ከአንድ በላይ ናቸው። ፍፁም የቢዝነስ ስትራቴጂ የሚባል ነገርም የለም። ትክክለኛ የሚባል አንድ ስራ ብቻም እንዲሁ።
ሁሉም ተረቶች ናቸው። እውነታው ይሄ ነው። በአንድ እርምጃ ትጀምራለህ፤ በየደረጃው እያስተካከልክ ትጓዛለህ፡፡ አለም የበለጠ ውስብስብ እየሆነች በሄደች ቁጥር መነሻ ነጥብህ ጠቃሚነቱን እያጣ ይሄዳል። ስለዚህ “በፍፁም ስሪትህ” ላይ ኃይልህን አታባክን፤ በስራም ቢሆን፣ በግል ሕይወትም ቢሆን፡፡ ከዚያ ይልቅ በአግባቡ እየሰሩ ያልሆኑ ነገሮችን ማስተካከልን ተማር፤ ተለማመድ። ይህንንም በፍጥነት እና ያለ ምንም የጥፋተኝነት ስሜት አድርገው፡፡
✍️ሮልፍ ዶብሊ
📚The art of clearly thinking
#share
@Human_intelligence
👍 41❤ 24🙏 5👏 2😢 2
የስምና የዝና ከርቸሌ
ከሚከተሉት መካከል የትኛውን ትመርጣለህ? በዓለም ላይ አንደኛ ጎበዝ ሆነህ እንደ አንደኛ ደደብ መታየት ወይስ የመጨረሻ ደደብ ሆነህ እንደ አንደኛ ጎበዝ መታየት?
ዋረን ቡፌት በሌላ አገላለፅ እንዲህ ያስቀምጠዋል። “ዓለም ሁሉ ማፍቀር የማይችል እያለህ ጎበዝ - አፍቃሪ መሆን ይሻልሃል ወይስ አንተ ፍቅር የማይገባህ ሰው ሆነህ - እያለ ዓለም በሙሉ ጎበዝ አፍቃሪ ቢልህ?” ይህንን በመመርመር ውስጥ ቡፌት ለጥሩ ሕይወት አንጓ ከሆኑ ነገሮች መካከል የሆነውን አንድ ነጥብ ያነሳል፡፡ ይህም በውስጥ ግምገማ (inner scorecard) እና በውጪ ግምገማ (outer scorecard) መካከል ያለው ልዩነት ነው፡፡
ላንተ ወሳኙ የትኛው ነው? “አንተ ራስህን እንዴት ነው የምታየው” የሚለው ነው። ወይስ “ሌሎች ሰዎች አንተን እንዴት ነው። የሚያዩህ” የሚለው?.. ትኩረትህ አንተ በራስህ ምን እንደምታደርግ በማስብ ፈንታ “ዓለም ስለኔ ምን ይላል” በሚለው ላይ ከሆነ የውጪ ግምገማ(outer scorecard) አፍቃሪ መሆንህ ይታወቃል፡፡ ይህም ጥሩ ሕይወትን የማበላሻ አንዱ መንገድ ነው፡፡
የሌሎች ሰዎች አስተያየት ያለው ጥቅም አንተ “አለው” ብለህ ከምታስበው በታች የወረደ ነው። ይህ በድንጋይ ዘመን የቀረ ነገር ነው፡፡ ሰዎች አንተን በአድናቆት ሰማይ ቢያስነኩህ ወይም በትችት ከትቢያ ቢደባልቁህ ይህ በሕይወትህ ላይ የሚኖረው እውነተኛ ተፅዕኖ አንተ ለራስህ ከሚሰማህ ኩራትና ሀፍረት አንፃር በጣም ዝቅተኛ ነው፡፡
ስለዚህ ራስህን ነፃ አውጣ፡፡ ይህንን ማድረግ ያለብህ ደግሞ ስለ ሶስት ምክንያቶች ነው፡፡ አንደኛ ይህ በስሜት የመዘፈቅ ሕይወት በአግባቡ እየመራህ የምትቀበለው አይሆንም፡፡ ወደድክም ጠላህም በጊዜ ሂደት ክብርና ዝናህን በአግባቡ መቆጣጠር አትችልም፡፡ ጂያኒ ኢጅኔሊን እንዲህ ይላል፡- “እያረጀህ ስትሄድ የሚገባህንና ትክክለኛውን ክብር (reputation) ታገኛለህ፡፡ ሰዎችን ለጊዜው ልታታልል ትችላለህ፤ በሕይወት ዘመን ሁሉ እንደሸወድክ መኖር ግን አትችልም፡፡”
ሁለተኛ በክብርና በዝና (prestige and reputation) ላይ ትኩረት ማድረግ (በትክክል ደስተኛ የሚያደርገን ነገር ምንድን ነው?› - የሚለውን አረዳዳችንን ይረብሻል፡፡ ሶስተኛ ያስጨንቀናል፡፡ ስለሆነም ይህ ለጥሩ ሕይወት ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው ነገር ነው፡፡
- እንደዛሬው ዘመን “ሰዎች ስለኛ ምን ይላሉ?” የሚለው ጭንቀት ጎልቶ የታየበት ወቅት የለም፡፡ ዴቪድ ብሩክስ እንዲህ ይላል “ማህበራዊ የመገናኛ ብዙሃን ሰዎችን ወደ ትንንሽ የብራንድ አስተዳዳሪነት ቀይሯቸዋል። ሰዎች ዛሬ ፌስ ቡክን፣ ቲውተርን፣ አጭር መልዕክትን እና ኢንስታግራምን እየተጠቀሙ የተጋነነ ውጫዊ ማንነትን ለመፍጠር ሲታትሩ ይውላሉ፡፡” ብሩክ
በፌስቡክ ላይ የምናገኛቸው የመጋራት (share) የመውደድ (like) እና ሌሎችም ግብረ መልስ መስጫዎች ሰዎች ለሰዎች ያላቸውን አረዳድ እንዲያንፀባርቁ የተቀረፁ ናቸው፡፡ በዚህ መንገድ ለሰዎች የምንሰጣቸው ግብረ መልሶች ደግሞ ፌስ ቡክ ላይ ባየነው መጠን እንጂ እውነተኛ ማንነታቸውን አውቀን የማይሆንበት እድል ሰፊ ነው፡፡ አንድ ጊዜ በዚህ መረብ ከተጠለፍክ ጥሰህ ለመውጣትና ጥሩ ሕይወትን ለመምራት ቀላል አይሆንልህም፡፡
#ትምህርት፡- ጭብጡ ምንም ይሁን ምን ሰዎች ስላንተ ሊፅፉና ሊያወሩ ይችላሉ። ከኋላህ እየተከታተሉ የሚያንሾካሹኩ ሰዎችም አይጠፉም። በውዳሴ ሊያሞካሹህ ወይም በትችት ሊኮንኑህ ይችላሉ። አንተ ይህንን መቆጣጠር አትችልም። ጥሩው ነገር ደግሞ መቆጣጠርም የሌለብህ መሆኑ ነው፡፡ ፖለቲከኛ ወይም ዝነኛ ሰው ካልሆንክ በስተቀር ገቢህ በማስታወቂያ ላይ የተመሰረተ አይሆንም፡፡ እንደዚህ ከሆነ ደግሞ ስለዝናና ክብር (reputation) አትጨነቅ፡ ከመወደድና ከመውደድ ውጣ። ራስህን ጎግል ላይ አትፈልግ። ከዚያ ይልቅ የሆነ ነገር ሥራ።
ቡፌት እንዲህ ይላል- “እኔ ደስ የሚለኝን ነገር ግን ሌሎች ሰዎች የማይወዱትን ነገር ባደርግ ደስተኛ ነኝ፡፡ ነገር ግን እኔ የሰራሁትን ነገር ሌሎች ሰዎች ቢያደንቁልኝም፣ እኔ ግን የማልረካበት ከሆነ ደስተኛ አልሆንም።” ይህ የውስጥ ግምገማ (inner scorecard) ትክክለኛ አገላለፅ ነው። ስለዚህ በዚህ ላይ አተኩር። የውጪ አድናቆቶችንና ወቀሳዎችን ዝቅ ባለ ስሜት እያችው።
✍️ሮልፍ ዶብሊ
የስብዕና ልህቀት
@Human_intelligence
@Human_intelligence
👍 56❤ 11👏 4
Фото недоступноПоказать в Telegram
ዲሲፕሊን!
“በምታልሙት ሕልም እና በእጃችሁ ሊገባ በሚገባው እውነታ መካከል ያለው ርቀት መጠሪያ ስሙ ዲሲፕሊን ይባላል” (Paulo Coelho)
ዲሲፕሊን የሌለው ሕልም፣ በምንም ያህል ተነሳሽነት (motivation) ቢጀመርም ከቅዠት ቀጠና አልፎ የመሄድ አቅም የለው፡፡
ዲሲፕሊን ማለት አንድን ማድረግ ያለብኝን ነገር ስሜቴ ቢፈቅድም ባይፈቅድም መደረግ ስላለበት ብቻ ማድረግ ማለት ነው፡፡ ማንኛውም ችሎታና ብቃት ከዲሲፕሊን ውጪ ከንቱ ነው፡፡ ምክንያቱም ዲሲፕሊን ከሌለኝ ምንም እንኳ የማድረጉ ብቃት ቢኖረኝና በነገሩ ባምንበትም ያንን ነገር ማድረግ ያስቸግረኛል፡፡ በሌላ አባባል ዲሲፕሊን ከሌለኝ መልካም ልማድን ለማዳበር ፈጽሞ አልችልም፡፡
ሕይወቴን በዲሲፕሊን ካልመራሁ የምተገብረውን ነገር የሚወስንልኝ ያመንኩበት መርህ ሳይሆን የእለቱ “ሙድ” ይሆናል፡፡ ይህ እንዳይሆን ራሳችንን ለመምራት ጤናማ የሆነን ዲሲፕሊን ማዳበር የግድ ነው፡፡
የስብዕና ልህቀት
👍 97❤ 16👏 2🔥 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
በሌላው ጫማ መሆን
አንድን ሰው በትክክል ለመረዳት በሱ ቦታ ብሆን ኖሮ ምን ይሰማኝ ነበር ብለህ ማሰብ አለብህ። አንዳንድ ነገሮችን በሌሎች ጫማ ውስጥ ሆነህ እስካለየሀቸው ድረስ ልትረዳቸው አትችልም። እናም በሌሎች ጫማ ሆነህ የሰዎችን ስሜት ለመረዳት ሞክር። በሕይወት ውስጥ ባሉ ጠቃሚ ግንኙነቶችህ ውስጥ ሁሉ ተጠቀምበት፡፡ ከቤተሰቦችህ ጋር፣ ከሰራተኞችህ ጋር ወይም ከመራጮችህ ጋር ሊሆን ይችላል፡፡ የሚና መቀያየር (role reversa) የጋራ መግባባትን ለመፍጠር የሚሆን ቀላልና ፈጣን ስልት ነው። አንደ ለማኝ ለብሶ የሚያስተዳድረው ህዝብ ውስጥ በመግባት ችግራቸውን ለመረዳት እንደጣረው ንጉስ ሁን።
የስብዕና ልህቀት
#share
@Human_Intelligence
@Human_Intelligence
👍 42❤ 12😢 3🔥 1🤔 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
ትናንት
-
የጎረቤት ጓዳ ... እንዳይሆን አድርጎ ... አመሳቅሏል ሲሉህ
ስቀህ ነበር አሉ ... በዚህ ክፉ ዜና ... ነግበኔን ዘንግተህ
~
ዛሬ
-
የሩቅ ያልከው ዜና ... ሲያደባ ቆይቶ ... ጎጆህ ተሰይሟል
ትንኝ ያልከው እንከን ... በጊዜ ባትገድለው ... ከዝሆን ጠብድሏል
~
ለነገ...
-
የክፋትህ እርሾ ... ውርስ ሆኖ እንዳይዘልቅ ... ከልጅ ልጅህ ታዛ
እጠብ ልቡናህን ... ፍካ ከጽልመትህ ... የፍቅር ስም ግዛ።
~~~
ደምስ ሰይፉ
የስብዕና ልህቀት
👍 53❤ 14😢 1
ማን ይቀስቅሰን?...
---
ደምስ ሰይፉ
እንደ ማሕበረሰብ አንቀላፍተናል… ጥልቅ እንቅልፍ ውስጥ ነን… ለሞት የቀረበ እንቅልፍ… ችግሩ ማንቀላፋታችንን አናውቅም… ማንቀላፋታችንን ስላላወቅን የተኛንበትንም አናውቅም… ማንቀላፋታችን ደግሞ በሌባ አስደፍሮናል… ችግሩ መሰረቃችንን አናውቅም… ወይም ግድ የለንም… የተዘረፍነው ግን አማናዊነት ነው… እውነተኛውን ማንነት!!… ስንነቃ እንደምን እንደነግጥ ይሆን?...
---
“Race is a lazy byproduct of not knowing your true self” ― Shaun S. Lott
___
የሰውን ልጅ እጅግ ከሚያሳንሱ ነገሮች ዋነኛው ምናልባትም ትልቁ ጎሰኝነት ይመስለኛል... ጎሰኝነት ከሁዳድ ጋርዮሽ የመዳፍ ቁርስራሽ የሚያስመርጥ እብደት ነው... የሰው ልጅ የሁዳድ ጋርዮሽ Space ሲሆን የመዳፍ ቁርስራሹ ደግሞ መንደርተኝነቱን የሚታቀፍበት ጎሳዊ ቅርጫት ነው... ስፔስ ላይ ቅርጫትን አኑሮ ማሰብ ጣና ሃይቅ ላይ አንዲት የጤፍ ፍሬ አስቀምጦ ከማሰብም በላይ ከባድ ነው...
___
ስለ [Multi verses] የሚያትተው የ Parallel universe ቲዎሪ እስከዛሬ ከምናውቀው በላይ ሌሎች ብዙ ቨርሶች ስፔስ ላይ እንዳሉ ሲያትት ሺህ ምንተሺህ ፕላኔቶች ሕዋውን እንደሞሉ እንረዳለን... ከዚህ አንፃር የኛይቱ ምድር ስላለንባት ግዙፍ ትምሰል እንጂ ከሌሎቹ እልፍ አዕላፍ ፕላኔቶች ጋር ስትተያይ እዚህ ግባ የሚባል መጠን ልኬት የላትም...
___
የሰው ልጅ ግን ከምድርም፣ ከቨርሶችም ከራሱ ከስፔስም ይልቃል፤ በፈራሽ በስባሽ ሥጋ የማይመተር፣ በጊዜና ቦታ የማይሰፈር ታላቅ ማንነት ባለቤት ነውና... ይህን ጽሩይ ማንነት ግን ሁሉ አይረዳውም ሁሉ አይገነዘበውም፤ አብዛኛው በጠፊ ጥላው ላይ ተመስጧልና...
___
“You are here to enable the divine purpose of the Universe to unfold. That is how important you are!” ~ Eckhart Tolle
___
እውነታው የስብዕናችን ግዝፈት ልክ አልባነቱን አመልካች ቢሆንም በመንደርተኝነት መጨፈናችን ልክና ገደብ ከሌለው ሕዋ አንፃር የድቃቂ አቧራን ያህል ዓይን የማትቆረቁረውን ምድርን ወደ ሌሎች ብናኞች የመከፋፈል ክፋት ውስጥ ዶሎናል... ችግሩ በዚህ ቢቆም መልካም ነበር፤ ቅንስናሹ ውስጥ 'ሌሎች' እንዲኖሩ የምንፈቅድበት መስፈሪያ ደግሞ አለን... የኔ ወገን፣ የኔ ዘር፣ የኔ ምንትስ... ወዘተ የሚያስብል ህመም...
___
እርግጥ የቋንቋ መኖር እውነት ነው... የጎሳ መኖር ግን ቅዠት ነው፤ በምንም አታረጋግጠውም... ታዲያ እንዴት ነው እኛና ሌሎች ለማለት የምንጠቀመው?... አማራ፣ ኦሮሞ ወይም ሲዳማነት በላብራቶሪ ውስጥ የሚረጋገጥ ነገር የለውም... ደምህ [A፣ B ፣ AB እና O] የሚል የወል ስም እንጂ ጉራጌ፣ ጋሞ፣ ትግሬ፣ አልያም ወላይታ የሚያሰኝ ንጥረ ነገር የለውም... 'እኔ ምንትስ ነኝ፣ እከሌ እንዲያ ነው' ስትል ቋንቋን፣ በአንድ አካባቢ መገኘትንና ትውስታን መሰረት ከማድረግህ ውጪ ምን ተጨባጭ ማስረጃ አለህ?...
___
የፍልስፍና ፕሮፌሰሩ David Livingstone Smith, “Less Than Human: Why We Demean, Enslave, and Exterminate Others” በተሰኘ ተሸላሚ መጽሐፉ ስለ ዘረኝነት ሲጽፍ “The folk notion of race is very much an artificial construction.” ብሏል…
---
እንግዲህ ቋንቋ እውቀት ነው - ማንም ይማረዋል... አንድ አካባቢ መገኘትም አጋጣሚ ነው - ማን አውቆ ይመርጠዋል?... የቆዳ ቀለም ለየአህጉሩ የተሰጠ የአየር ሁኔታ ግልባጭ ነው - በቆዳው ውስጥ ያለውን የ melanin መጠን ማን መወሰን ይችላል?... እስኪ ንገረኝ - ‘ነኝ’ የምትለውን ነገድ የሆንከው በምንህ ነው?... ራስህን ከኔ የነጠልከው ምን ይዘህ ነው?... ልዩ ልዩ ቋንቋና ይትባሃል ፈጥረን ውበት ከመጨመራችን ውጭ በሰውነታችን መሃል 'ልዩነትን' የሚያሳይ ምን ነገር አለን?... ነገዴ ግንባሬ ላይ ተጽፎ ይሆን እንዴ?...
___
ወዳጆቼ... ይህ የመንደርተኝነት ህመም በዚህ ከቀጠለ የእግር መቆሚያ ሁሉ ሊያሳጣን ይችላል... ለአማናዊ ማንነቱ ኢትዮጵያዊ ዜግነት የማይመጥነውን፣ አፍሪካዊነት የማይስተካከለውን፣ ምድር እንኳ የማትፎካከረውን ለብቻው ዩኒቨርስ የሆነን ሰው እንዴት 'መንደርህን ፈልግ' ትሉታላችሁ?... “You are here on earth to unearth who on earth you are.” ― Eric Micha'el Leventhal
___
@bridgethoughts
@Human_Intelligence
@Human_Intelligence
👍 32👏 12❤ 2
ራስን ከፍ አድርጎ የማየት ኢጎ
በህይወት ስቃይ ና ችግሮች ውስጥ ስንሆን በችግሮቻችን የበለጠ አቅመቢስነት የሚሰማን እንሆናለን፡፡ በዚህም ከእነዚያ ችግሮች ለማምለጥና ያንን ለማካካስ ራሳችንን ከፍ አድርጎ ማየት እናዳብራለን፡፡ ይህ ራስን ከፍ አድርጎ ማየት ከእነዚህ በአንዱ መንገድ ይሰራል፡፡
1. እኔ በጣም አሪፍ ነኝ ሌሎቻችሁ ግን ደባሪዎች ናችሁ ስለዚህ የተለየ እንክብካቤ ያስፈልገኛል፡፡
2. እኔ የምረባ አይደለሁም ሌሎቻችሁ
ግን አሪፎች ስለሆናችሁ የተለየ እንክብካቤ ያስፈልገኛል የሚሉ ናቸው፡፡
እነዚህ ሀሳቦች በውጪ ሲታዩ ተቃራኒ አስተሳሰብ፣ ውስጡ ግን ተመሳሳይ ራስ ወዳድነት ያለባቸው ናቸው፡፡ በእርግጥ ራሳቸውን ከፍ አድርገው የሚያዩ ሰዎች በሁለቱ መካከል ሲዋዥቁ ይታያሉ፡፡ ወይ እነርሱ ከአለም ሁሉ በላይ ናቸው አለዚያም ደግሞ አለም ሁሉ ከእነርሱ በላይ ነው፡፡ ይህም መዋዠቅ የሚከሰተው የሆነ ቀን ወይም ያለባቸውን ሱስ እያስታገሱ ባሉባት ቅጽበት ይሆናል፡፡
ብዙ ሰዎች ከንቱ በሆነው ለራሳቸው በሚሰጡት ከፍተኛ ክብር የተነሳ በራሳቸው ፍቅር የወደቁ እንዲሁም በጣም ለፍላፊ በመሆናቸው ከሌላው ሰው በቀላሉ መለየት ይችላሉ።በቀላሉ መለየት የማይችሉት ለራሳቸው ከፍተኛ ክብር የሚሰጡ ሆነው ነገር ግን ዝቅተኛ እንደሆኑና ለአለም የማይጠቅሙ እንደሆኑ የሚሰማቸውን ነው፡፡
በሕይወት ውስጥ ሁሉም ነገር አንተን ለመጉዳት የሚደረግና ያለማቋረጥ ተጠቂ የሚያደርግህ አድርጎ መተርጎም ልክ ተቃራኒውን እንደማድረግ ያህል ራስ ወዳድነት ነው፡፡ አንደኛው ምንም አይነት ችግር የሌለበት ሆኖ አንደኛው ደግሞ ሊቀረፍ የማይችል ችግር አለበት የሚል እምነት ማዳበር የዚያኑ ያህል በከፍተኛ ደረጃ ከንቱ የሆነ ራስን ከፍ አድርጎ የማየት ነገር ይፈልጋል፡፡ እውነታው በሕይወት ውስጥ የግል ችግር የሚባል ነገር አለመኖሩ ነው፡፡ የሆነ ችግር ካለብህ፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሌሎች ሰዎችም ከዚህ ቀደም የዚያ አይነት ችግር ነበረባቸው ወይም አሁን አለባቸው አለበለዚያም ወደፊት ይኖርባቸዋል፡፡ የዚያ ችግር ተጠቂዎች ምናልባትም አንተ የምታውቃቸው ሰዎች ሊሆኑም ይችላሉ፡፡ ይህ መሆኑ ግን ችግሩን አያሳንሰውም ወይም የሚጎዳ የመሆኑን መጠን አይቀንሰውም፡፡ ይህ ማለት በአንዳንድ ሁኔታዎች ተጠቂ ላትሆን ትችላለህ ማለትም ሳይሆን ይህ ማለት አንተ የተለየህ አይደለህም ማለት ነው፡፡
በአብዛኛው ችግሮችን ለመፍታት የመጀመሪያውና በጣም አስፈላጊ የሆነው እርምጃ፣ አንተና የአንተ ችግሮች በችግሮቹ ከባድነት ወይም በሚያስከትሉት ስቃይ ተጠቃሚዎች አለመሆናችሁን መረዳት ነው፡፡
ራስን ከፍ አድርጎ የማየት ችግር
አንድ ጊዜ ሰዎች በዙሪያቸው የሚከናወነው ሁሉ ራስን ትልቅ አድርጎ የሚያሳይ እንደሆነ ያለማቋረጥ እንዲገምቱ የሚያደርግ አስተሳሰብ ካዳበሩ፣ እነርሱን ከዚያ ውስጥ ሰብሮ ማውጣት በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ እነርሱን ለማስረዳት የሚደረግ ሙከራ ሁሉ ለእነርሱ የእነርሱን ታላቅነት፣ ምን ያህል ጎበዝ፣ ተሰጥኦ ያላቸው፣ መልከ መልካሞችና ስኬታማ መሆናቸውን መሸከም ባለመቻል የሚመጣ ጥቃት ተደርጎ ይታያል፡፡
ራሳቸውን ከፍ ያሉ እንደሆኑ የሚሰማቸው ሰዎች፣ በሕይወት ውስጥ ያሉት ሁኔታዎች ሁሉ ለእነርሱ ታላቅነት ወይ አድናቆት ወይ ጥቃት የተሰሩ ናቸው ብለው ያምናሉ፡፡ የሆነ ጥሩ ነገር ካጋጠማቸው እነርሱ በሰሩት አሪፍ ነገር ምክንያት ነው፡፡ መጥፎ ነገር ካጋጠማቸው የሆነ ሰው ቀንቶ ሊጎዳቸው ሞክሮ ነው፡፡ ራስን ከፍ አድርጎ ማየት ዘላቂነት የለውም፡፡ እንደዚህ አይነት ሰዎች የእነርሱን የበላይነት ስሜት በሚያጠናክር በየትኛውም ነገር ራሳቸውን ያሞኛሉ፡፡ ምንም ያህል ዋጋ ቢያስከፍልም፣ አንዳንድ ጊዜ በዙሪያቸው ላሉ ሰዎች አካላዊና ስሜታዊ ጉዳት የሚያስከትል ቢሆንም የአእምሮ እይታቸውን ይከላከላሉ፡፡
ለራሳቸው ከንቱ የሆነ ከፍተኛ ግምት የሚሰጡ ሰዎች ለራሳቸው ችግሮች በግልፅና በታማኝነት እውቅና መስጠት ስለማይችሉ ህይወታቸውን ዘላቂ ወይም ትርጉም ባለው ሁኔታ ማሻሻል አይችሉም፡፡ እንደዚህ ያሉ ከፍተኛ ክህደት እያሳደዱና ታላላቅ የክህደት ደረጃዎች እያከማቹ ለመኖር የተተው ናቸው፡፡
ግን በመጨረሻ እውነቱ ይወጣና የተቀበሩት ችግሮች ሁሉ እንደገና ራሳቸውን ግልፅ ሲያደረጉ ከባድ የህይወት ምስቅልቅል ውስጥ ይገባሉ።
📚- The subtle art of not giving a fuck
✍️ - Mark manson
@Zephilosophy
👍 42❤ 6🙏 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
ፍቅር የሰብዓዊነት ቅኔ የሚነበብበት መድብል ፣የተፈጥሮ ዕንቁ ሚስጥር ፈትሸን የምናገኝበት ጥራዝ፣ የገሀዱን ዓለም ብርሃን ሻማ የምናገኝበት መቅረዝ፣ የህልውናችን አንፀባራቂ መስታወት ናት።
ፍቅር ቀዬ ና ጎጥ ሳይከትረን ውቅያኖስና አድማስ ሳያግደን በአንድ የምንታይባት ገፅና ያለንን በበጎነት የምንቸርባት የሰጡንን በቅንነት የምንቀበልበት የአዕምሮ በረከትና የህሊና ማዕድ ናት።
የስብዕና ልህቀት
Join👇👇👇
@Human_Intelligence
@Human_Intelligence
❤ 57👍 20🥰 5
Фото недоступноПоказать в Telegram
ሕይወት የምትጀምረው መቼ ነው?
ሁለት ሰዎች በአንድ ጉዳይ ላይ ይከራከሩ ነበር፡፡ አንዱ፣ “ሕይወት የምትጀምረው ልክ አንድ ጽንስ በተጸነሰበት ቅጽፈት ነው” በማለት ያንን እምነቱን በግለት ያስተጋባል፡፡
ሌላኛው ደግሞ፣ “አይደለም! ሕይወት የምትጀምረው የተጸነሰው ልጅ የመጀመሪያውን ትንፋሽ ወደመተንፈስ ደረጃ ሲደርስ ነው” በማለት የተጋጋለ ምላሹን ይናገራል፡፡
ይህንን ሃሳብ ሳይለቁ ለሰዓታት ሲከራከሩ የተመለከተ አንድ ሰው እያዋዛ አንድን ትምህርት ትቶላቸው አለፈ፣ “ሁለታችሁም ተሳስታችኋል፤ ሕይወት የምትጀምረው ሰው የተፈጠረለትን ዓላማውን ሲያውቅና ያንን መከተል ሲጀምር ነው”!!!
ዓላማችንን እንወቅ! በግለት እንከታተለው! እንኑረው!
የስብዕና ልህቀት
@Human_intelligence
❤ 68👍 35👏 3
Фото недоступноПоказать в Telegram
የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ
ራስን ከሌላው ሰው ጋር ማነጻጸር ቀንደኛው የደስታና የሰላም ሌባ ነው፡፡ የዚህ ራስን ከሌላው ሰው ጋር የማነጻጸር አራጋቢ ደግሞ ማሕበራ ሚዲያ ነው፡፡
ማሕበራዊ ሚዲያ ያደረገብን ነገር ቢኖር ይህ ነው፡፡ ሰዎች ያላቸውን ጉድለት በመሸሸግ እኛ እንድናየው የሚፈልጉትን የተቀባባ ሁኔታ ብቻ ነጥለው ያቀርቡልናል፡፡ እነሱ በሚዲያ ነጥለው ያቀረቡትን “የተሻለ” ነገራቸውን ካየን በኋላ መለስ ብለን ስለራሳችን ከምናውቀው “ዝቅተኛው” ማንነት ጋር ማነጻጸር እንጀምራለን፡፡ በውጤቱም የእኛ ሕይወት ምን ያህል ወደኋላ እንደቀረ ማሰብ እንጀምራለን፡፡ ይህ አጉልና የተዛባ እሳቤ፣ የምንፈልገው ነገር ምን እንሆነ እከማናውቀው ድረስ እንድንቅበጠበጥና ደስታ-ቢስ እንድንሆን ያደርናል፡፡
ፍቅረኛ ብናገኝ አንረጋጋ፣ ገንዘብ ብናገኝ አንረካ፣ ብንለብስ ያማረብን አይመስለን . . . የሌለውንና የማይደረስበትን እንደፈለግን እንኖራለን፡፡
ምናልባት ስሜት ቀስቃሽ (Sensational) ከሆኑት ማሕበራዊ ገጾች አጉል ተጽእኖ ረገብ ብንልና የራሳችንን የሕይወት ግብ፣ አቅጣጫና ከፍታ ከራሳችን ራእይ አንጻር ብናወጣው ቅጥ ያጣው የውስጥ ስሜታችን ይረጋጋ ይሆናል፡፡
ዶ/ር እዮብ ማሞ
የስብዕና ልህቀት
@Human_Intelligence
@Human_Intelligence
👍 57❤ 12👏 5
Фото недоступноПоказать в Telegram
አራቱ ስህተቶቻችን
• አጥብቀን መያዝ ያለብንን ነገር በቀላሉ መልቀቃችን፣ በቶሎ መልቀቅ የሚገባንን ነገር ደግሞ አጥብቀን መያዛችን!!!
• ሰርተን ማግኘት የሚገባንን ነገር በነጻ መጠበቃችን፣ በነጻ የተሰጠንን ነገር ሰርተን አለማሳደጋችን!!!
• የማይፈልጉንንና የማይጠቅሙንን ሰዎች መከታተላችን፣ የሚፈልጉንንና የሚጠቅሙንን ሰዎች ችላ ማለታችን!!!
• መናገር በሚገባን ጊዜና ሁኔታ ላይ ዝም ማለታችን፣ ዝም ማለት በሚገባን ጊዜና ሁኔታ ላይ መናገራችን!!!
ዶ/ር እዮብ ማሞ
Join👇👇
@Human_intelligence
@Human_intelligence
👍 125❤ 18👏 7🤔 2
Фото недоступноПоказать в Telegram
-----
የተራማጅ አሸን - የተጓዥ ዘመሚት ... በዘጋው መንገድ ላይ
የትናንት አሻራ - የክፋት ትራፊ ... ምርግ መስሎ ብታይ
...
ፍኖት እንደሌለው - ምርጫ አልባ ተስፋ ቢስ ... አትሁን አደራ
ነባሩን ጣጥለህ - ዛሬን የሚመስል... አዲስ መንገድ ስራ!!
-----
ደምስ ሰይፉ
@Human_intelligence
🔥 28👍 17❤ 2
Фото недоступноПоказать в Telegram
አሻራ…
--------
የሆነ ጊዜ ላይ ደርሰህ ከቤተሰብ እስከ ማሕበረሰብ፣ ከመንደር እስከ ሃገር በሚዘረጋው የኑረት ጎዳና ላይ አሻራህን የሚያሳይ አንዳች እውነት ትፈልጋለህ... እናም እንዲህ ብለህ ትጠይቃለህ - 'በእኔ መኖር ምክንያት ምን ተቀየረ?'... አበርክቶህ ምንም ያህል ቢሆን በተቀበልከው ኖረህ ስታልፍ ለሌሎች የምታቀብለው ተክቶህ እንዲቀጥል ትሻለህና 'መዋጮዬ ወዴት አለ?' ማለትህ አይቀርም...
___
ዛሬ የምትኖረውን ኑሮ እንድትኖር ትናንት ዋጋ የከፈሉ ሰዎች ነበሩ... ለነዚህ ሰዎች ወደኋላ ሄደህ ብድር አትመልስ ይሆናል... ወደፊት ሄዶ ዕዳህን የሚከፍል ስንቅ ማኖር ግን ግዴታህ ነው... አልያማ ሰው ኖሮ ካልጠቀመ ሄዶ እኮ አያጎድልም - ባለዕዳነቱን አይሰርዝም እንጂ!!...
___
የመኖር ውሉ በራስ ታዛ መድመቅ ብቻ አይደለም... የሌሎችንም ማገር ማጥበቅ እንጂ... በበጎ ቃል - የታመመ ልብ ትፈውሳለህ፣ የጎበጠ ሞራል ታቀናለህ... በፍቅር ኃይል - ቂም በቀል ትሽራለህ፣ ጥላቻን ትንዳለህ... ሰው ነህና ብዙ የምትሰጠው ይኖርሃል...
___
ብቻ... በራስ ዛቢያ ከጦዙበት እልፍ ዓመት - ሌሎችን የቀላቀሉበት ክራሞት፣ ለብቻ ከኖሩት የዕድሜ ብዛት - ለትውልድ ያኖሩት ጥቂት ብልሃት የበለጠ ዋጋ አለው...
___
ሞትን ለምን እንደምንፈራ አስበህ ታውቃለህ? - ኖረን ስለማናውቅ ነው!!
___
"Even death is not to be feared by one who has lived wisely." ~ Gautama Buddha
ደምስ ሰይፉ
___
#share
የስብዕና ልህቀት
@Human_intelligence
👍 63❤ 7👏 3🤔 1
