127 753
مشترکین
-1624 ساعت
-287 روز
-65030 روز
آرشیو پست ها
Photo unavailableShow in Telegram
ዩኒቨርስቲዎቹ ተማሪዎችን ሙሉ በሙሉ መቀበል እንዳልቻሉ አስታወቁ
የመቐለ እና አዲግራት ዩኒቨርስቲ በትግራይ ክልል አልፎ አልፎ በሚስተዋሉ፤ የፀጥታ ስጋቶች እና በተያያዥ ገፊ ምክንያቶች ትምህርት ሚኒስቴር በ2018 ዓ.ም የመደበላቸውን የተማሪዎች ቁጥር ሙሉ በሙሉ መቀበል አለመቻላቸውን አስታውቀዋል።
ለዚህ ምክንያት የሆነው ደግሞ "አንዳንዶቹ ተማሪዎች በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከፍለው መማር የሚችሉ ስለሆኑ እንዲሁም፣ አንዳንዶቹ ደግሞ በቤተሰብ ጫና ምክንያት ርቀው እንዳይሄዱ ስለሚደረጉ ሊሆን ይችላል" ሲሉ ጠቁመዋል።
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
Photo unavailableShow in Telegram
ራያ ዩኒቨርሲቲ ሁለት የፈጠራ እና የምርምር ዲጂታላይዜሽን ሥራዎች አስመርቋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በተቋሙ መምህራንና ተመራማሪዎች የበለጸጉ ሁለት የቴክኖሎጂ ሽግግር ስራዎችን ይፋ አድርጓል፡፡
ግእዝን በሞባይል መማር የሚያስችል 'ፍኖተ-ግእዝ' የተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ እና የምርምር ፖርታል በዩኒቨርሲው ይፋ የተደረጉ የቴክኖሎጂ ሽግግር ስራዎች ናቸው፡፡
ፍኖተ-ግእዝ የሞባይል መተግበሪያ የእጅ ስልክን በመጠቀም መሰረታዊ የግእዝ ቋንቋ ክህሎቶችን ለማበልፀግ የሚያግዝ የሞባይል አፕሊኬሽን መሆኑ ተገልጿል።
የምርምር ፖርታሉ የዩኒቨርሲቲውን የምርምር ውጤቶች ዲጅታል ቋት፣ የምርምር መረጃዎች አስተዳደር ስርዓት እንዲሁም የዩኒቨርሲቲውን የሳይንስና ልማት ጆርናል (RJSD) አንድ ላይ የሚያጠቃልል ነው ተብሏል፡፡
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
Photo unavailableShow in Telegram
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ መደበኛ የአማርኛ መዝገበ ቃላት እያዘጋጀ ነው፡፡
ዩኒቨርሲቲው “የአማርኛ ልሳነ ዋሕድ መዝገበ ቃላት ዝግጅት ጥናት ንድፍ“ በሚል የውይይት መርሐግብር በቅርቡ አካሒዷል፡፡
በዩኒቨርሲቲው የሚዘጋጀው መዝገበ ቃላት ዘመኑን የዋጀ፣ ከሳይንስና ቴክኖሎጂ ጋር የተቀመረ እና ዲጂታልንም ታሳቢ ያደረገ እንደሚሆን ተገልጿል፡፡
የመጀመሪያው የአማርኛ መዝገበ ቃላት እ.አ.አ. በ1698 ዓ.ም የታተመ ሲሆን፤ የከሣቴ ብርሃን አማርኛ መዝገበ ቃላትን ጨምሮ በተለያዩ ጊዚያት የአማርኛ ቋንቋ መዝገበ ቃላት ታትመዋል፡፡
የሳይንስና ቴክኖሎጂ እንግሊዝኛ አማርኛ መዝገበ ቃላት በቅርቡ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ለህትመት መብቃቱ ይታወሳል፡፡
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
Photo unavailableShow in Telegram
የሰላሌ ዩኒቨርስቲ ከ 3ሺህ በላይ ለሚሆኑ አቅመ ደካማ የሕብረተሠብ ክፍሎች የነፃ የሕግ አገልግሎት መስጠቱን አስታወቀ
የሰላሌ ዩኒቨርስቲ የሕግ አገልግሎት ለሚያስፈልጋቸው ሶስት ሺ አራት መቶ ዘጠና ስድስት አቅመ ደካማ የማህበረሰብ አካላት የተለያዩ የሕግ አገልግሎት ሰጥቷል።
የዩኒቨርስቲ የሕግ አገልግሎት ዲን አቶ አቤል ከተማ እንደገለፁት የነፃ የሕግ አገልግሎቱ የተሰጠው አቅመ ዳካማ ለሆኑ ፣ በእድሜ ለገፉ፣ ጥቃት ለደረሠባቸው ሴቶች ና ሕፃናት፣በከፍተኛ ሕመም ለሚገኙ እና በማረሚያ ቤት ሆነው የፍርድ ሂደታቸውን ለሚከታተሉ ታራሚዎች የነፃ የሕግ አገልግሎት ነው ብለዋል።
በዚህም ለሁለት ሺህ ሠባት መቶ ሀምሳ ስድስት ወንዶች እንዲሁም ለሰባት መቶ አርባ ሴቶች አገልግሎቱ ተሰጥቷል። በነፃ አጉልግሎቱ ስድስት መቶ ዘጠና ሁለት ሺህ ብር ከወጪ ማዳን የተቻለ ሲሆን የሰላሌ ዪኒቨርስቲ በስሩ የሚተዳደሩ አራት ቋሚ የሕግ አገልግሎት መስጫና እና አንድ ተንቀሳቃሽ የሕግ ማዕከል አቋቁሞ በመንቀሣቀስ በተለየ መልኩ በሕፃናት እና ሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን እንደዚሁም ያለ እድሜ ጋብቻ፣የቤተሰብ ግጭቶች እና ትንኮሳዎች ላይ ሰፊ የሕግ መሰረት ያደረገ አገልግሎት መስጠቱን አቶ አቤል ከተማ ጨምረው ገልፀዋል::
ፆታዊ ጥቃትን በተመለከተ ከጋብቻ ውጭ የተወለዱ እና የሚጣሉ ሕፃናት ማቆያ ለመገንባት ከፍትህ አካላት ጋር የጋራ ስምምነት የተደረሠ ሲሆን ባለፈው አመት ሶስት ሕፃናት ተጥለው የተገኙትን የሠላሌ ዩኒቨርስቲ ተረክቦ በአበበች ጐበና ካምፖሱ ባለው ጊዚያዊ ማቆያ በማቆየት በሕጋዊ መንገድ ለጉዲፈቻ ተሰጥተዋል።
በዩኒቨርስቲ ውስጥ የሴት ተማሪዎች ላይ የሚደርሰውን ትንኮሳ እና ጥቃት ለመከላከልም የተቋቋመ ኮሚቴ ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረገ ሲሆን በአጠቃላይ የፍትሕ አካላት ጋር በቅንጅት ለመስራት የተደረገው ስምምነት ከፍተኛ ውጤት እንደሚያመጣም ተመላክቷል።
#ዳጉ_ጆርናል
Photo unavailableShow in Telegram
በ2018 ዓ.ም ለሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርት ከሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ወደ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ዝውውር ያመለከታችሁ ተማሪዎች በሙሉ መሀል ሜዳ ካምፓስ የተመደባችሁ መሆኑን ተቋሙ ገልጿል፡፡
በ2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርት ለመከታተል የተመደባችሁ ተማሪዎች ሪፖርት ማድረጊያ ቀናት ታህሳስ 02 እና 03/2018 ዓ.ም መሆኑ ይታወቃል፡፡
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
Photo unavailableShow in Telegram
#AdigratUniversity
በ2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር ለሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርት ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ታህሳስ 06 እና 07/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
ትምህርት ታህሳስ 08/2018 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል።
ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
➫ የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
➫ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➫ አራት መጠኑ 3x4 የሆነ የቅርብ ጊዜ ፎቶግራፍ፣
➫ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN)፣
➫ ብሔራዊ መታወቂያ (Fayda)፣
➫ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ የትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ፡፡
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
Photo unavailableShow in Telegram
ትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በላከው ሰርኩላር የስራ ዕድል ፈጠራ ልማት (CEED) ማዕከላት ያሉበትን ደረጃ ሪፖርት እነዲልኩ ጠይቋል፡፡
የመንግሥት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ2018 ዓ.ም የስራ ዕድል ፈጠራ ልማት (CEED) ማዕከላትን በማደራጀት ለተማሪዎች እና ሠራተኞች ተከታታይነት እና ተገቢነት ያላቸውን የማማከርና የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች እንዲሰጡ እንደሚጠበቅ ሚኒስቴሩ አስታውሷል፡፡
ስለሆነም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ባቋቋሙት ማዕከላት ስር እስካሁን የተሠሩ ስራዎችን ለመገምገም እንዲቻል፤ የተላከላችሁን የጉግል አድራሻ በመጠቀም የምታገኙትን መጠይቅ በመሙላት እስከ ህዳር 30/2018 ዓ.ም ድረስ በኢሜይል አድራሻ tamiratk95@gmail.com ሪፖርት እንድትልኩ ተብሏል፡፡
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
Photo unavailableShow in Telegram
#WallagaUniversity
በ2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ለሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርት የተመደባችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ታህሳስ 02 እና 03/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
ትምህርት የሚጀምረው ታህሳስ 06/2018 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል፡፡
የምዝገባ ቦታ፡-
➫ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ጊምቢ ካምፓስ፣
➫ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ወንዶች ከፊደል A-D እና ሴቶች ከፊደል A-H ሻምቡ ካምፓስ እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ወንዶች ከፊደል E-Z እና ሴቶች ከፊደል I-Z ዋናው ግቢ ነቀምቴ ከተማ
ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
➫ የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ካርድ ዋናውና ኮፒው፣
➫ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➫ አራት መጠኑ 3x4 የሆነ ፎቶግራፍ፣
➫ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ የትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ።
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
Photo unavailableShow in Telegram
#MaddaWalabuUniversity
በ2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር ለሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርት መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ታህሳስ 06 እና 07/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
ትምህርት ታህሳስ 08/2018 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል።
ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
➫ ከ8-12ኛ ክፍል ያሉ የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውና ኮፒው፣
➫ መጠኑ 3x4 የሆነ ፎቶግራፍ፣
➫ የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ፣
➫ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ እና የትራስ ልብስ፡፡
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
Photo unavailableShow in Telegram
በኬንያ የትልልቅ ድርጅቶች ስራ አስፈፃሚዎች ከመምህራን በ214 እጥፍ የተሻለ ክፍያ ያገኛሉ ተባለ።
የኬንያ አስር ግዙፍ ድርጅቶች ዋና ስራ አስፈፃሚዎች በአማካይ ከኬንያ መምህራን በ214 እጥፍ የተሻለ ክፍያ እንደሚያገኙ ኦክስፋም ኬንያ አስታውቋል።
ኦክስፋም አክሎም፥ ለዋና ስራ አስፈፃሚዎቹ የሚደረገው አማካይ የክፍያ ጭማሪ ከአስተማሪዎቹ የ6 አመት ደመወዝ ጋር እኩል መሆኑንም ገልጿል።
በተጨማሪ በኦክስፋም ሪፖርት በኬንያ የሚገኙ 125 ሃብታሞች ከ77 በመቶው ወይም 42.6 ሚሊየን ህዝብ የበለጠ ሃብት እንዳላቸው ተመላክቷል።
ከ2019-2023 ባለው ጊዜም 1% የሚሆኑት ሃብታሞች የሃገሪቱን ሁለት አምስተኛ ሃብት እንደያዙና የነዚህ 1% ሃብታሞች ሃብት ከቀሩት 99% አንፃር በእጥፍ ማደጉ ተነግሯል።
እነዚህ 1% ሃብታሞችም የሃገሪቱን የፋይናንስ ሃብት 78% መያዛቸው ሲነገር ከ2015 ወዲህም በከፍተኛ ድህነት የሚኖሩ ሰዎች ቁጥር በ7 ሚሊየን መጨመሩ ተነግሯል።
በ125ቱ የኬንያ ሃብታሞች የተያዘው ሃብት ወደ 100 ሽልንግ የመገበያያ ገንዘብ ቢቀየር ሙሉ የናይሮቢ ግዛትን እንደሚሸፍን የኦክስፋም ሪፖርት አሳይቷል።
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
Photo unavailableShow in Telegram
#ጥቆማ
ጤና ሚኒስቴር የማርበርግ ቫይረስ ዝግጁነት #የኦንላይን ትምህርት ለጤና ባለሙያዎች መስጠት ጀምሯል።
ይመዝገቡ 👇
https://cpd.moh.gov.et/cpd/course/view.php?id=112
የኦንላይን ስልጠናውን ይውሰዱ! ዝግጁነትዎን ይጨምሩ!
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
Photo unavailableShow in Telegram
Join Ethiopia's premier competitive programming hackathon.
A full-day, on-site event dedicated to advanced problem-solving, data structures and algorithms.
Form a team of three and compete in divisions open to both advanced (Elite) and intermediate (Open) coders for national recognition and exciting prizes! 🏆
🗓 ቅዳሜ, ኅዳር 27 2018 (December 6, 2025)
⏰ 3፡00 - 11፡00 ሰአት (9:00 AM – 5:00 PM)
📍 CapStone ALX Tech Hub, Lideta
🔗 Register now: https://luma.com/9pobz8sd
#ALXEthiopia #CodeLeagueEthiopia #CompetitiveProgramming #DSA #dohardthings #ALXAfrica #lifeatALX
Photo unavailableShow in Telegram
#WolkiteUniversity
በ2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር ለሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርት ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ታህሳስ 06 እና 07/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
➫ የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
➫ የ8ኛ ክፍል ካርድ ዋናውና ኮፒው፣
➫ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➫ ሁለት መጠኑ 3x4 የሆነ ፎቶግራፍ፣
➫ ብሔራዊ የፋይዳ መታወቂያ (National ID)፣
➫ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ እና የትራስ ልብስ፡፡
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
Photo unavailableShow in Telegram
#AksumUniversity
በ2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር ለሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርት ወደ አክሱም ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ታህሳስ 06 እና 07/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
በተጠቀሱት ቀናት አክሱም ከተማ በሚገኘው የዩኒቨርሲቲው ዋናው ግቢ በአካል በመገኘት ሪፖርት እንድታደርጉ ተብሏል።
ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
➫ የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ካርድ ዋናውና ኮፒው፣
➫ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➫ አራት 3x4 የሆነ የቅርብ ፎቶግራፍ፣
➫ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ እና የትራስ ልብስ፡፡
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
Photo unavailableShow in Telegram
ተጨማሪ!
ትምህርት ሚኒስቴር በተለያዩ የሙያ ዘርፎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቀው የመምህርነት ሙያን መቀላቀል ለሚፈልጉ የአንድ ዓመት ስልጠና ለመስጠት ምዝገባ እያደረገ መሆኑ ይታወቃል፡፡
ስልጠናው ይሰጣል ከተባለባቸው አምስት ዩኒቨርሲቲዎች በተጨማሪ በመቐለ ዩኒቨርሲቲ እንደሚሰጥ ተገልጿል።
የመቐለ ዩኒቨርሲቲ መመዝገቢያ ሊንክ 👇 https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdRwj89yQ50AiUeZZeDe8tr8aJ5GQZO4B0IqUVJzJJCNJzWPQ/viewform
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
