Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
Open in Telegram
ነጻነት ለህዝባችን - ብልጽግና ለአገራችን! Bilisummaan uummata keenyaaf - badhaadhinni biyya keenyaaf! Freedom to our People – Prosperity to our Nation!
Show more162 898
Subscribers
-124 hours
+1537 days
+51830 days
Posts Archive
በቡድን 20 ጉባኤ ያደረኳቸውን ሁለትዮሽ ውይይቶቼ የመጨረሻ የሆነውን ውይይት ከጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጂኦርጂያ ሜሎኒ ጋር በአለምአቀፍ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ብሎም በቁልፍ የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ አተኩረን አከናውነናል።
The last of my bilaterals at the G20 Summit was with Prime Minister Giorgia Meloni, where we discussed global and regional affairs, as well as key bilateral issues between our countries.
ከብራዚል ፕሬዝደንት ሉዊዝ ኢናችዮ ሉላ ደ ሲልቫ ጋር ጥሩ ውይይት አድርገናል። ውይይታችን በኢኮኖሚ እና ዘላቂ የመሠረተ ልማት ጉዳዮች ላይ አተኩረን የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን የምናጠናክርባቸውን እድሎች አስመልክቶ የተካሄደ ነበር። ብራዚል በቅርቡ የተካሄደው የCOP30 አስተናጋጅ ሀገር እንደመሆኗ COP32ን በኢትዮጵያ ስናዘጋጅ ከብራዚል የምንወስደው ብዙ ጠቃሚ ልምዶች አሉ። የአለም የአየር ንብረት ጥበቃ ሥራን የሚያራምድ በሚገባ የተሰናዳ መስተንግዶ እንዲኖረን ከልምዶች የተገኙ ሃሳቦችን መለዋወጡን አጠናክረን ለመቀጠል አቅደናል።
Good meeting with Brazilian President Luiz Inácio Lula da Silva. We discussed opportunities to strengthen bilateral cooperation, focusing on economic development and sustainable infrastructure. As the recent COP30 host, Brazil has many valuable lessons to share with Ethiopia as we prepare to host COP32. We plan to consolidate these insights to ensure a well-prepared and impactful hosting that advances global climate action.
Photo unavailableShow in Telegram
ከካፍ ፕሬዝደንት ከዶክተር ፓትሪስ ሞትሲፒ በአፍሪካ እግር ኳስ እና ኢትዮጵያ በእድገቱ ስለሚኖራት ሚና ፍሬያማ ውይይት አድርገናል። ለወጣቶች እድገት፣ የስፖርት መሠረተ ልማት ብሎም የአፍሪካን እግርኳስ በአለም መድረክ ለማላቅ ከካፍ ጋር ስለሚኖረን ትብብር ተወያይተናል።
I had a productive discussion this morning with CAF President Dr. Patrice Motsepe on the state of African football and Ethiopia’s role in its development. Highlighted our commitment to youth development, infrastructure, and strengthening partnerships with CAF to elevate African football on the global stage.
ከቡድን 20 ጉባኤ ጎን ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ጋር ውይይት አድርገናል። ውይይታችን የባለብዙ ወገን ግንኙነታችንን ለማጠናከር ብሎም እንደ የአየር ንብረት ጥበቃ ሥራ፣ ሰላም እና ፀጥታ፣ ዘላቂ ልማት ያሉ የጋራ አለምአቀፋዊ ትኩረታችንን በምናጠናክርበት መንገድ ላይ ያጠነጠነ ነበር። ኢትዮጵያ የCOP32 አስተናጋጅ ሀገር እንደመሆኗ መጠን ሊደረግ ስለሚችለው ድጋፍም ተወያይተናል።
I held a productive bilateral meeting with UN Secretary-General António Guterres on the sidelines of the G20 Summit, where we discussed strengthening multilateral cooperation and advancing shared global priorities, including climate action, peace and security, and sustainable development. We also discussed support for Ethiopia as the host of COP32 in 2027.
04:03
Video unavailableShow in Telegram
Africa’s economic rise is underway, taking shape in our cities, farms, factories, and digital ecosystems. To unlock its full potential, reform must drive investment, and investment must drive shared growth.
4.77 MB
ከአለም ባንክ ፕሬዝደንት እና ከኢትዮጵያ መልካም ወዳጅ አጄይ ባንጋ ጋር መወያየት ሁልጊዜም ቢሆን አስደሳች ነው። በመካሄድ ላይ ስላሉት በአለም ባንክ ቡድን ለኢትዮጵያ የሚደረጉ ድጋፎች ዙሪያ ተወያይተናል። ይኸውም በጤና፣ በኃይል ምንጭ እና የአየር ንብረት ጥበቃ የልማት ፕሮጀክቶች የገንዘብ ድጋፍ ጉዳይን የተመለከተ ነበር።
Always a great pleasure meeting with Ajay Banga, President of the World Bank and good friend of #Ethiopia. We discussed the World Bank Group’s ongoing support to Ethiopia, including financing development projects in health, energy, and climate.
ከዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታመር ጋር ተገናኝተን በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ጠንካራውን እና ለረጅም ዘመናት የቆየውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደፊት ማራመድ በማስፈለጉ ላይ ተወያይተናል።
Met with Sir Keir Starmer, Prime Minister of the United Kingdom for exchanges on the need to take forward the strong and longstanding bilateral relations between two countries.
በቡድን 20 የመሪዎች ጉባኤ ከኢንዶኔዥያ ምክትል ፕሬዝደንት ጊብራን ራክቡሚንግ ራካ ጋር መልካም ውይይት አድርገናል። በሁለቱም ሀገሮቻችን ቅድሚያ በምንሰጠው በንግድ እና በምግብ ሉዓላዊነት ላይ ባተኮረ የግብርና ማዘመን ሥራ ትብብራችንን ለማጠናከር የሚያስችሉ መንገዶች ላይ ተነጋግረናል።
Good conversation with Vice President Gibran Rakabuming Raka of Indonesia at the G20 Summit. We explored ways to strengthen the cooperation of the two countries on trade and agricultural modernization with a focus on food sovereignty, which is a priority for both countries.
በቡድን ሃያ መሪዎች ስብሰባ ፍሬያማ እና ትርጉም ያላቸው ተጨማሪ ውይይቶችን ከህንድ፣ ቬይትናም፣ ደቡብ ኮሪያ እና አውስትራሊያ መሪዎች ጋር አካሂደናል።
A productive and substantive day at the G20 Leaders’ Summit with additional engagements with fellow leaders from India, Vietnam, South Korea and Australia as well.
ከኖርዌይ ጠቅላይ ሚኒስትር ጆናስ ጋህር ስተር ጋር በአየር ንብረት ጥበቃ ሥራ ትብብር፣ የጋራ ትኩረት በሚሹ የባለብዙወገን ጉዳዮች ብሎም ትብብራችንን በሚያጠናክሩ እና ዘላቂ እድገትን በሚያሳድጉ የኢንቨስትመንት እድሎች ላይ ተወያይተናል።
Had a constructive meeting with Norway’s Prime Minister Jonas Gahr Støre, focusing on climate action cooperation, multilateral issues of shared concern, and opportunities for investment to strengthen our partnership and drive sustainable growth.
የጀርመን ቻንሰለር ፍሬድሪክ ሜርዝ ጋር ተገናኝተን ተወያይተናል። ውይይታችን በቁልፍ የጋራ ፍላጎት ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሲሆን ትስስራችንን ለማጠናከር የሚረዱ መንገዶችን ለመፈለግ ያለንን ፍላጎት ገልጸናል።
Good to meet with Chancellor Friedrich Merz today. We exchanged views on key areas of mutual interest and expressed our shared intention to explore ways to strengthen ties.
የኢትዮጵያ እና ፈረንሳይ ግንኙነት እየተከናወኑ ባሉ ትብብሮች መጠናከሩን ቀጥሏል። በዚህ ረገድም ከፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር ትብብሮቻችን ስላሉበት ደረጃ ተነጋግረናል።
Ethiopia-France relations continue to strengthen through ongoing engagements. Accordingly, President Macron and I had the opportunity to meet on the sidelines of the G20 Leaders’ Summit for a productive catch-up.
የኢትዮ-አውሮፓ ኅብረት ግንኙነት ለማላቅ ከአውሮፓ ኅብረት ምክርቤት ፕሬዝደንት አንቶኒዮ ኮስታ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደናል። በተለያዩ ዘርፎች ትብብራችንን የበለጠ ለማጠናከር አቋማችንን እንደገና አጽንተናል።
Building on Ethio-EU existing relations, I held a bilateral meeting with António Costa, President of the European Council. We reaffirmed our commitment to deepening cooperation between Ethiopia and the European Union across multiple areas.
ከፊንላንድ ፕሬዝደንት አሌክሳንደር ስተብ ጋር በቀጠናዊ፣ ባለብዙ ወገን ትብብር፣ እና በሁለትዮሽ ግንኙነት፣ የአየር ንብረት ጥበቃ ሥራ እና በኢትዮጵያ በተከፈተው የኢኮኖሚ ምኅዳር ስላሉ የኢንቨስትመንት እድሎች ተወያይተናል። ውይይታችን የሁለትዮሽ ትስስራችንን እና የጋራ ጥቅም ትብብሮችን በማጠናከር ላይ ያለንን አቋም ያጠናከረም ነበር።
Met with President Alexander Stubb of Finland for bilateral discussions on regional issues, multilateral cooperation, and bilateral cooperation in education, climate action, and investment opportunities in Ethiopia amid the country’s economic opening. The meeting reaffirmed our commitment to strengthen bilateral ties and advance mutually beneficial collaboration.
ከቱርክዬ ፕሬዝደንት ጣይብ ኤርዶዋን ጋር በኢኮኖሚ፣ የባሕል ወዳጅነት ግንኙነት፣ ዘላቂ ልማት፣ በአየር ንብረት ጥበቃ ሥራዎችን በሚያካትቱ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ውይይት አድርገናል።
Productive meeting with President Recep Tayyip Erdoğan of Türkiye on a range of topics, including economic and cultural partnerships, sustainable development, and cooperation on climate action.
ከቡድን 20 ጉባኤ ጎን የአቡዳቢ ልዑል አልጋ ወራሽ ሼክ ካሌድ ቢን መሃሙድ ቢን ዛይድ አልናህያን ጋር የመወያየት እድል አግኝተናል። ውይይታችን ስትራቴጂካዊ ትብብራችንን በማጠናከር ለበለጠ የጋራ ርምጃ እድሎችን መመልከት ላይ ያተኮረ ነበር።
On the sidelines of the G20 Summit, I also had the honor of meeting with Sheikh Khaled bin Mohamed bin Zayed Al Nahyan, Crown Prince of Abu Dhabi. The discussions focused on strengthening strategic partnerships and opportunities for collaboration.
ከአዲሱ የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝደንት ዶክተር ሲዲ ኡልድ ታህ ጋር ተገናኝተን ተወያይተናል። ውይይታችን ባንኩ በመላው አፍሪካ አካታች እድገት እንዲኖር የሚያደርገውን ወሳኝ ሚና ያጠናከረ ነበር።
It was a pleasure to sit down today with the new President of the African Development Bank (AfDB), Dr. Sidi Ould Tah. Our discussion reinforced the vital role the Bank continues to play in advancing inclusive growth and opportunity across Africa.
በቡድን 20 ጉባኤ ጎን ለጎን ከIMF ፕሬዝደንት ክሪስታሊና ጂኦርጂየቫ ጋር በአለም አቀፍ የኢኮኖሚ አዝማሚያዎች ፣ በሀገራችን የኢኮኖሚ ሪፎርም እንዲሁም ዘላቂ እና አካታች እድገትን ለመደገፍ ትብብራችንን ለማጠናከር ስላሉ እድሎች ላይ ተወያይተናል። ለIMF የዘለቀ ግንኙነት ምስጋናዬን እያቀረብኩ የጋራ ትኩረቶቻችንን ለመፈፀም መነሳታችንንም እገልጻለሁ።
At the G20 Summit, I held a constructive bilateral meeting with IMF President Kristalina Georgieva during which we discussed global economic trends, our national economic reforms, and opportunities to strengthen cooperation in support of sustainable and inclusive growth.
I appreciate the IMF’s continued partnership and look forward to advancing our shared priorities.
በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ዋዜማ የአስተናጋጃችን ሀገር ፕሬዝደንት ከሆኑት ሲሪል ራማፎሳ ጋር ተገናኝተናል። ታሪካዊው የጂ20 ጉባኤ በአፍሪካ ምድር እንደመሰናዳቱ በተለያዩ ጉዳዮች እንዲሁም በጉባኤው የአፍሪካ የወል ድምጽ እና የጋራ ፍላጎት የሚቀርብበትን ሁኔታ ተወያይተናል።
On the eve of the G20 Leaders Summit, I met with our host, President Cyril Ramaphosa, to discuss a range of issues, including the importance of presenting a common Africa voice and shared priorities, especially as this historic G20 is being hosted on African soil.
